Monday, July 30, 2012

የጋብቻ አባወራነት

Read in PDF
በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ
መግቢያ፡-
የጋብቻ ቅንጅት” በተባለው በአንደኛ ጽሑፋችን በመጀመሪያ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደ ተገለጠው የጋብቻ ቅንጅት እግዚአብሔር በሁለት ባልና ሚስት መካከል የሚገኝበት ቅንጅት ነው፡፡ በቅንጅቱም ባልና ሚስት ፊት ለፊት ተያይተው የልብ መግባባት እንደሚኖራቸው ተመልክተናል፡፡ በአንድ በኩል የባልና ሚስት እኩልነት እግዚአብሔር እነርሱን በመፍጠሩና በመውደዱ ለክብሩ እንዲኖሩ በዓለም በማስቀመጡ ተገልጾአል፡፡ በሌላ በኩል ግን በጋብቻ ውስጥ የሁለቱንም ኀላፊነት ስንመለከት ጐላ ያለ ልዩነት ይታያል፡፡ በመካከላቸው ያለው የፍቅር ግንኙት እንደ እግዚአብሔር ዕቅድ እንዲሠራ ባልና ሚስት በፈጣሪያቸው ከመጀመሪያ በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን መሠረታዊ ልዩነት እንዲያስተውሉ ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ በጋብቻ ውስጥ ያለው አባወራነት ይህን ልዩነት እንዴት እንደሚያብራራ አሁን ልንመለከት እንችላለን፡፡

የአባወራነት ሕግ
የክርስቶስ ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ፡፡ ይህ የሐዋርያው ጳውሎስ ቃል ሊያስደነግጠን ይችል ይሆናል፤ ነገር ግን ይህ ቃል የሚያመለክተን አባወራነት የተጀመረው በዔድን ገነት ውስጥ ሳይሆን ከዘላለም በሥላሴ ዘንድ ነው፡፡ እኛም ስለ ሥላሴ ስንናገር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንላለን እንጂ ወልድ አብ መንፈስ ቅዱስ አንልም፡፡ በመለኮታዊ ባሕርይ አንድና እኩል ሲሆኑ በተግባራቸው የሚገለጥና በአባወራነት የተመሠረተ ቅደም ተከተል አላቸው፡፡ በምድራዊ አባትና ልጅ መካከል ያለውን ያንጸባርቃል፡፡  

Sunday, July 22, 2012

“እኔ ጐስቋላ ሰው ነኝ … ማን ያድነኛል?” (ሮሜ 7፥24)

                 Read IN PDF                                                              (በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ)
ካለፈው የቀጠለ
እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ሲመለከት ጻድቅ የሆነ አንድ ሰው ስንኳ ከመካከላችን እንዳልተገኘ፥ ኀጢአት ያልተመረተበት የሰውነት ክፍልም በእያንዳንዳችን እንደ ሌለ የሚገልጹትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ባለፈው ዕትም ተመልክተናል (መዝ. 13፥1-3)። የዛሬው ዕትም ደግሞ ሰው መበላሸት ከመፈጠሩ ጀምሮ እንዳልሆነ ያስነብበናል።

የሰው አፈጣጠር እንዴት ነበር?

መቼም እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደ ነበረ መጽሐፍ ቅዱስ በቅድሚያ ያረጋግጥልናል (ዘፍ. 1፥4፡10፡12፡18፡21፡25፡31)።

እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ነበረ ሲባል፥ መልካም ከነበረው ፍጥረት አንዱ ሰው እንደ ሆነ ግልጽ ነው። እንዲያውም “መልካም” የሚል ገደብ የተበጀለትን የየዕለቱን ፍጥረት መመዘኛ በማለፍ “እጅግ መልካም” የሚል እመርታን የሚያሳይ ዐዲስ የመመዘኛ ወሰን የተገኘው ሰው ከተፈጠረና የፍጥረት ገዥ ሆኖ ከተቀመጠ በኋላ ነበር (ዘፍ. 1፥31)።

Thursday, July 19, 2012

ልዩ ልዩ





በመሠረተ እምነት
ስለ ክርስቶስ መካከለኛነት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሰጡትን ምስክርነት በመልክ በመልኩ በማቅረብ አንዳንዶች ዛሬ ቢያስተባብሉትም፥ የክርስቶስ መካከለኛነት ግን በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የታወቀ መሆኑን ያስረዳል፡፡


የዘመን ምስክር
የቀደሙ አባቶቻችን የሠሩትን መልካም ሥራና ያሳዩትን በጎ አርኣያነት የሚዘክረው ይህ ዐምድ፥ የአባ እስጢፋኖስንና የደቂቀ አስጢፋኖስን የተጋድሎ ታሪክ፥ በዚህ ዘመን እየተነሡ ካሉ አከራካሪ ጉዳዮች ጋር በማዋሐድ፥ ስለወንጌልና በምድራችን እንዲመጣ ይፈልጉት ስለነበረው ተሐድሶ ያለፉበትን መንገድ ያስቃኛል፡፡