Friday, February 8, 2013

ልዩ ልዩ


ከማኅበረ በኲር

1.    አመሠራረቱ

ወንጌል በሀገራችን እንደተሰበከ ከተቋቋሙት ቀደምት ማኅበራት አንዱ ማኅበረ በኵር ነበረ፡፡ አሁንም “በኲረ አኀው (የምእመናን ወንድሞች አለቃ)” በሆነው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ማኅበረ በኲር የቀድሞውን ስምና ትውፊት ወርሶ ተቋቁሟል፡፡

2.   የእምነት መግለጫ
የማኅበረ በኲር ትምህርተ እምነት መሠረቱ፥ ግድግዳው፥ ጣሪያውና ጒልላቱ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ጥንታውን ሊቃውንት ከመጽሐፍ ቅዱስ በማውጣጣትና አሰባስቦ በማዘጋጀት እምነታቸውን የገለጹባቸው፡-

ሀ. የሐዋርያት እምነት መግለጫ፥
ለ. የኒቅያ የእምነት መግለጫ (ጸሎተ ሃይማኖት)፥
ሐ. የሐዋርያት አመክንዮ እና
መ. የአትናቴዎስ የእምነት መግለጫ የተባሉትን ማኅበረ በኲር በእምነት መግለጫነታቸው ይቀበላቸዋል፡፡

3.  አስተምህሮት
የማኅበረ በኲር አስተምህሮት በጮራ መጽሔት በግልጽ ይተላለፋል፡፡ የምእመናንን ዐይን መግለጥ እንደ ጦር የሚፈሩት፥ ለራሳቸው የሚያምኑትን፥ የኔ የሚሉትን በማስተማር ፈንታ ባልተሰጣቸው ውክልና ስለሌላው መናገር የሚያዘወትሩት ትውልደ አውጣኪ ከሚነዙት መርዘኛ ወሬ የማኅበረ በኲር አስተምህሮት የተለየ ነው፡፡

4.   ግንኙነት
“በአብ የተጀመረች እምነት ወደ ወልድ ታደርሳለች፥ በመንፈስ ቅዱስም ትፈጸማለች፡፡ ሃይማኖት እንተ እም ኀበ አብ ተወጥነት ኀበ ወልድ ታበጽሕ፥ ወኀበ መንፈስ ቅዱስ ትትፌጸም፡፡” እያሉ በአብ፥ በወልድ፥ በመንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ መሆን ከሚያምኑ ሁሉ ጋር የመንፈስ አንድነት እንዳለው ማኅበሩ ያምናል፡፡ ስለ ሆነም፥ ጒድለትና ጭማሪ የሌለበትን ሦስትነትና ፍጹምነት ያለውን የኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝነት ይመሰክራል፡፡


(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበ)

1 comment:

  1. God bless you ,may GOD use you to reform The ETOC to the original form.

    ReplyDelete