Wednesday, May 2, 2012

ልዩ ልዩ


Read in PDF 
በጮራ ቊጥር 3 ላይ የቀረበ

ለፈገግታ



ገበሬው ባለው አንድ በሬ ከሌሎችም አቀናጅቶ ማረሱ ከፍተኛ ችግር ይፈጥርበትና ያንን ሸጦ ሁለት መለስተኛ በሬዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡ በሬው ለዐይን ሞላ ብሎ ጥሩ ዋጋ እንዲያወጣለት በማሰብ ጭድ በገፍ ሲያበላው ይሰነብትና ለገበያ ያቀርበዋል፡፡ 

በሬውን ሊገዛ የመጣ ነጋዴም የበሬው አቋም ከሩቅ ይስበውና ጠጋ ብሎ ተዟዙሮ በደንብ ይመለከተዋል፤ በመጨረሻም ከወደ ሆዱ ጐሸም እያደረገ፤ «ባለ ጭድ ዋጋውስ?» ይለዋል በሽሙጥ፡፡ 

ነገሩ የገባው ገበሬም «ለጠንቋይ አይሸጥም» በማለት አጸፋውን መለሰለት ይባላል፡፡