Monday, August 13, 2012

ግጥም

Read in PDF
(በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ)
                                        
                                        የትግል ምዕራፍ

በቀጭኑ መንገድ ሰዎች ባልበዙበት
መሰናክልና እንቅፋት ባለበት
ጀምረህ እንደ ሆን አቅንትህ መራመድ
ወደ ኋላ ሳትል ወደ ፊትህ ንጐድ፡፡

ጒዞህን ጀምረህ ጥቂት ዕልፍ ስትል
አለልህ እንቅፋት የሚጥር ለመጣል፡፡

አለልህ እርግጫ  አለልህ ኲርኲሙ
ሊጥልህ ይታገላል ሁሉም እንዳቅሙ፡፡

እርሱን ዐለፍ ብለህ በሥቃይ እንዳለህ
እምነት እሚፈታ ተራራ ታያለህ፡፡

ይህን ሁሉ ዐልፈህ መንገዱ ወለል ሲል
የመረረው ጒዞ ሲተካልህ በድል
ምዕራፉ ሲዘጋ ግፊውም ያከትማል፡፡

1 comment:

  1. God Bless! you. i like all your teachings because this teachings touch every Christians life and fills the shortage of Bible knowledge in the generation. stay Blessed!

    ReplyDelete