Thursday, May 1, 2014

አለቃ ነቅዐ ጥበብ

Read in PDF:- Aleka nekeatebebe
አለቃ ነቅዐ ጥበብና አገልግሎታቸው

ከነቅዐ ጥበብ

የአለቃ ነቅዐ ጥበብ አገልግሎት ከእልፍኛቸው ከወጣ ሰንብቷል፡፡ የወንጌል አገልግሎታቸው ለቤተ ሰብ ብቻ መሆኑ ቀርቶ የአካባቢውን ኅብረተ ሰብ የሚያቅፍ ሆኗል፡፡ በቤተ ክርስቲያን፥ በገበያ፥ በዕድር ስብሰባ፥ በልዩ ልዩ ሸንጎ ሁሉ የአለቃ ነቅዐ ጥበብ አገልግሎት ዜና ተስፋፍቶ ይወራል፡፡ “ጠበል ይረጫሉን?” አይ የለም የሰውን ውስጣዊ አካል ማየ ሕይወት በሆነ በእግዚአብሔር ቃል ይረጫሉ፥ ያጥባሉ እንጂ!” የሚለው ጥያቄና መልስ ከሕዝብ ለሕዝብ ሆኗል፡፡

“ኤጭ! ከአያት፥ ከቅድም አያት የወረስነውን ባህለ ሃይማኖታችንንና አድባራችንን፥ አውሌያችንን፥ ጨሌያችንን… አስማምተን ይዘን እንደ ቈየን መቀጠል ይበጃል እንጂ ከሰልባጅ ጋር የመጣ መጽሐፍ ቅዱስ አያዋጣንም” አለ ተቈርቋሪ መሳዩ የደብተራ ምንተስኖት ልጅ፡፡