Wednesday, January 30, 2013

ክርስትና በኢትዮጵያ



የእግዚአብሔር መንግሥት ታሪክ
በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበ

ካለፈው የቀጠለ

በሰሜንም በደቡብም ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ነገዶች የየራሳቸውን አምልኮት ይዘው እንደ ገቡ ሁሉ እስራኤላውያንም በብሉይ ኪዳን ላይ የተመሠረተውን አምልኮተ እግዚአብሔር ይዘው በየጊዜው ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል ስለ መባሉ ባለፈው ዕትም (ጮራ ቊ. 4) ላይ አስነብበናል፡፡

የአምልኮት መወራረስ የተለመደ ነውና እስራኤላውያንም በጋብቻ፥ በአሰፋፈር፥ በጉርብትና፥ በንግድ ልውውጥና በመሳሰለው አዛማጅ መንገድ ተባባሪና ተጣማሪ ለሆኗቸው ሌሎች ኢትዮጵያውያን ሀልዎተ እግዚአብሔርን ሳይሰብኩላቸው ሥርዐተ አምልኮታቸውንም ሳያስተምሯቸው እንዳልቀረ ከማሰብ የሚገታ ምክንያት አይኖርም፡፡

Saturday, January 26, 2013

መጽሐፍ ቅዱስ

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

በጮራ ቊጥር 4 ላይ የቀረበ
ኦሪት ዘፍጥረት 3፥1-13

መግቢያ
ሰው ይህን ምዕራፍ ካልተረዳ ጠቅላላውን የመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብ እንደዚሁም የዓለምንና የሰውን ሁኔታ ሊያስተውል አይችልም፤ ስለዚህ ከማንበብህ በፊት እግዚአብሔር ምስጢሩን እንዲገልጽልህ ጸልይ፡፡

ሰው እግዚአብሔር ካዘጋጀለት ክብር፥ ጸጋ፥ በረከትና ብፅዕና ወደቀ፡፡ የአዳም ታሪክ የእኛ ታሪክ ነው፡፡ በአዳም ውስጥ ሆነን (ተቈጥረን) ኀጢአት ሠራን፤ በእርሱ ሞትን (ሮሜ 5፥12፡15፡18፡19)፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን የአባታችንን ስሕተት ተከትለን በሰይጣን እየተሳሳትን በየጊዜው እንወድቃለን፡፡

Wednesday, January 23, 2013

ልዩ ልዩ



ስለ ተሐድሶ ጥያቄ አለኝ፤ ሃይማኖት ይታደሳልን?

በየትውልዱ የኖሩና ያለፉ ሰዎች ውቀውም ሆነ ሳያውቁ በዘመን ብዛት የሚፈጥሩት ልብ ወለድ ትምህርት እውነተኛውን የሃይማኖት አካል ያቈሽሸዋል፤ ይሸፍነዋል፤ ይቀብረዋልም፡፡ መቈፈርና የተቀበረውን ማውጣት፥ ቈሻሻውን ማስወገድና የሃይማኖትን ጥራት በእግዚአብሔር ቃል መጠበቅ ግብረ ተሐድሶ ነው፡፡ ለምሳሌ፥ ሰው ሥራ ውሎ ሲገባ፥ ከመኝታው ሲነሣ፥ ቈሻሻ ሲነካው፥ ሲደክመውና ሲያልበው ይታጠባል፡፡ በውሃና በሳሙና ቈሻሻውን አስወግዶ ራሱን ወደ ቀድሞ ንጽሕናው ይመልሰዋል፡፡ የመታጠቡም አስፈላጊነት በተፈጥሮ የታደለውን የአካሉን ቁመናና ቅርጽ    የውስጣዊ ብልቶቹንም ብዛትና አቀማመጥ ለመለወጥ አይደለም፤ ተፈጥሮውን ያበላሻውን ቈሻሻ በማስወገድ ጥንተ ተፈጥሮውን በንጽሕናና በጤንነት ተጠብቆ እንዲኖር ለማድረግ ነው እንጂ፡፡ ከግብረ ተሐድሶ አንዱ ይህን ይመስላል፡፡

(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበ)

Monday, January 21, 2013

ጋብቻ

የአብርሃምና የሣራ ጋብቻ
“የምድር ነገዶች ሁሉ በአንተ ይባረካሉ፡፡”
ዘፍ. 12፥3

እግዚአብሔር የደኅንነትን ዕቅድ ሲያዘጋጅ አንድ ቤተ ሰብ መረጠ። አብርሃምን ከዑር እንዲወጣ ሲጠራው እግዚአብሔር “የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ” ብሎ ተስፋ ሰጠው፡፡ እንግዲህ ቤተ ሰብ በእግዚአብሔር ሐሳብ ከፍ ያለ ዋጋ እንዳለው በዚህ እናያለን፡፡

የእግዚአብሔር ባሕርይ፥ የሰውም ሁኔታና የእምነት እውነታዎች ስላልተለወጡ፥ እኛም ምንም እንኳ በሌላው ዘመንና በተለየ ባህል ብንኖር ከአብርሃም ቤተ ሰብ የሚጠቅመንን ትምህርት ልንማር እንችላለን፡፡

Saturday, January 19, 2013

መጽሐፍ ቅዱስ


የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
(በጮራ ቊጥር 3 ላይ የቀረበ)
ኦሪት ዘፍጥረት 2

መግቢያ፤ ይህ ምዕራፍ የምዕራፍ አንድ ማሟያ ነው፡፡ ምዕራፍ አንድ እግዚአብሔር ዓለምን እንዴትና ለምን እንደ ፈጠረ ሲገልጥ ታላቅነቱንና በላይነቱን ያሳያል፡፡

ምዕራፍ ሁለትም እግዚአብሔር ለሰው አስፈላጊውን ሁሉ እንዳዘጋጀ ሲገልጥ ሰው በዓለም መኖር እንዴት እንደሚገባው ያሳያል፡፡ ምዕራፍ አንድ “እግዚአብሔር” ሲል በምዕራፍ ሁለት ብዙ ጊዜ “እግዚአብሔር አምላክ” ይላል፡፡ ይህም ፈጣሪያችን ለሰው ያለውን ፍቅርና ጠባቂነት ያመለክታል (ያተኲራል)፡፡ (ስለ እግዚአብሔር ስሞች “የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት” የተባለውን መጽሐፍ ተመልከት)

Thursday, January 17, 2013

የመዳን ትምህርት



(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበ)

ካለፈው የቀጠለ

አዳምና ሔዋን ኀጢአትን ከሠሩ በኋላ ከእግዚአብሔር ለመሰወር፥ ነውራቸውንም ለመሸፈን ሲሉ በቊጥቋጦ ውስጥ እንደ ታሸጉና የበለስንም ቅጠል በመስፋት እንደ ለበሱ ሁሉ፥ የእነርሱም ልጆችና የልጅ ልጆች እንደ እነርሱ የሚያደንቋቸውን የምድር ፍጥረታትንና የሰማይ ሰራዊትን ሲማጸኑ ረድኤትን ለማግኘት እንዳልተሳካላቸው ባለፈው ዕትም ያነበብነውን እናስታውሳለን (መዝ. 120/121፥1)፡፡

በዛሬው ዕትም ደግሞ በራሱም በአካባቢውም ከሚገኙ ግዙፋንና ረቂቃን ፍጥረታት ተስፋ ላላገኘ የሰው ዘር እግዚአብሔር በራሱ ዕቅድ የነደፈለትን የመዳን መንገድ ለማስነበብ የሚከተለው ቀርቧል፡፡

Tuesday, January 15, 2013

ልዩ ልዩ


ያንብቡኝ
(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበ)
በትልቁ መሶብ መጽሐፍ ቅዱሳችሁ
የሕይወት እንጀራ ቀርቦ ከፊታችሁ
       (የዮሐንስ ወንጌል 6፥47-64)

ከየቈሻሻው ውስጥ ምነው መልቀማችሁ?
                                  (መጽሐፈ ኢዮብ 15፥14-16፤ 25፥4-6)

አያጠግባችሁም፤ ጤናም አይሆናችሁ፡፡
                                               (ትንቢተ ኢሳይያስ 55፥1-3)

Monday, January 14, 2013

መጽሐፍ ቅዱስ


የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
(በጮራ ቊጥር 2 ላይ የቀረበ)
ዓለም ፍጥረት ኦሪት ዘፍጥረት 1 
እግዚአብሔር የፍጥረትን ታሪክ ለማን እንደ ገለጠ፥ ወይም መጀመሪያ ማን እንደ ጻፈው በመጽሐፍ ቅዱስ ባይገለጥም ከጥንት የመጣ፥ በዕብራይስጥ ቋንቋ የተጻፈ ለእግዚአብሔር ሕዝብም የተሰጠ፥ መሆኑ ግልጥ ነው፡፡

ይህንን ታሪክ ስናነብ አንዳንድ ነገሮችን መገንዘብ ያስፈልገናል፡፡

ሀ. በእስራኤል ዙሪያ የነበሩ አረማውያን ፀሓይን፥ ጨረቃንና፥ ሌሎች ብዙ ፍጥረታትን ያመልኩ ስለ ነበር የእግዚአብሔር ሕዝብ ስለ አምላካቸውና ስለ ፍጥረቱ በትክክል እንዲማሩ አስፈላጊ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ሰዎች ወደ ፀሓይና ጨረቃ በአምልኮት እንዳይመለከቱ ጸሓፊው “ትልቁ ብርሃን” ና “ትንሹ ብርሃን” እያለ እንዳስገነዘባቸው ይታያል፡፡

Sunday, January 13, 2013

ርእሰ አንቀጽ


ከፍሬአቸው ታውቁአቸዋላችሁ
(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበ)

ምሁር ነኝ የሚሉ አረጋዊ ከሰዎች ጋር ሲነጋገሩ፥ “የእኛን ሃይማኖት የሚያህል ፈጽሞ የለም” ብለው የማውራት ልምድ ተጠናውቷቸዋል፡፡ እንዲህም ሲናገሩ ስመ ሃይማኖታቸውን እየጠሩ ነው፡፡ ቅያሬ የሌለውና የተጋነነው ከቃል ንግግር በቀር የሕይወት ምስክርነት ያልነበረው ወሬአቸው ወዳጆቻቸውንና ቤተ ሰባቸውን ጭምር አሰልችቷቸው ኖሮአል፡፡

አንድ ቀን ከአንድ ወዳጃቸው ጋር ይጨዋወቱ ነበር፡፡ እንደ ተለመደው “የእኛን ሃይማኖት የሚያህል የለም፤ ብቻ ምን ያደርጋል” ሲሉ፤ በተከታዮች ብዛት ከሆነ የ… እምነት ተከታዮች ይባልጣሉኮ! አለና መለሰላቸው፡፡ ትልቋ ልጃቸው ግን አባባ የእኛ ሃይማኖት ካለማመን የሚለይበትን አንድ ነጥብ ቢነግሩኝ ብትላቸው ምን ለማለት እንደ ፈለገች አልተረዱላትም፡፡ ልጅቷ የመደነጋገር ምልክት በአባቷ ፊት ላይ እንዳየች በሌላ የአገላለጽ ዘዬ ልታስረዳቸው ሞከረች፡፡ አባቷም ሲረዱ በጣም ተቈጡ፡፡

Thursday, January 10, 2013

መጽሐፍ ቅዱስ


ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ጠቅላላ ዕውቀት
(በጮራ ቊጥር 4 ላይ የቀረበ) 
ከሁሉን መርምር

በአንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዝ በብሉይ ኪዳን መጨረሻ ከገጽ 721-1037 በሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዞች የማይገኙ መጻሕፍት በመጨመራቸው ተጨንቀውና ግራ ተጋብተው ያውቃሉን? “ተጨማሪ (ዲዮትሮካኖኒካል) የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት” በሚል የክፍል መጠሪያ የተጨመሩት መጻሕፍት 18 ናቸው፡፡ በውሳኔ የተጨመሩት መጻሕፍት የሚገኙበት ጥራዝ በአንዳንድ ሰዎች ዘንድ እንደ ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ ሲቈጠር፥ እነርሱ የሌሉበት ጥራዝ ግን “ጐደሎ መጽሐፍ ቅዱስ” ተብሎ ሲጠራ ተሰምቷል፡፡

መጠሪያቸው እንደሚያስረዳው እነዚህ ተጨማሪ መጻሕፍት ቀደም ሲል ከቅዱሳት መጻሕፍት ቊጥር ውጪ እንዲሆኑና በአዋልድነት እንዲጠሩ ያደረጓቸው አያሌ ታዋቂ ምክንያቶች መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ ምክንያቶቹ ከአዋልድ መጻሕፍቱ ጋር ታትመው ቢሆኑ ኑሮ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎችን ባላደናገሩ ነበር፡፡

Tuesday, January 8, 2013

አለቃ ነቅዐ ጥበብ


ጭውውት
(በጮራ ቊጥር 4 ላይ የቀረበ)


ከየትና ከየት ተገናኛችሁ? እንደ ምን ሰነበታችሁ? ግቡ፥ ግቡ እንጂ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ሁላችንም ከተለያየ አቅጣጫ ስንመጣ በርቀት ብንተያይም መድረሻችን አንድ መሆኑን የተረዳነው አሁን ነው፡፡ እንደ ምን ሰነበቱ? … እግዚአብሔር ይመስገን - አለቃ ነቅዐ ጥበብና እንግዶቹ የተለዋወጡት ሰላምታ፥

የአለቃ እልፍኝ በውስጡ ዙሪያውን መደብ የተሠራለትና አጐዛና ሰሌን የተነጠፈበት ስለ ነበረ ሁሉም እንዳገባባቸው ተቀመጡ፡፡ ሥራ በሌለበት የበዓል ቀን ብዙ ሰው ወደ ቤታቸው እየመጣ አብዛኛውን ጊዜ ስለ ነገረ ሃይማኖት ያልገባውን በመጠየቅ የሚያጠግብና የሚያረካ መልስ ስለሚያገኝ አለቃ ሰዎቹን ለምን መጣችሁ? አላሏቸውም፡፡

Tuesday, January 1, 2013

ጥያቄዎቻችሁና መልሶቻቸው



1ኛ ጥያቄ፥ ከእኅት ሐረገ ወይን፥ ጮራዎች መጽሐፍ ቅዱስ ስለ መልከ ጼዴቅ፥ “የስሙም ትርጓሜ በመጀመሪያ የጽድቅ ንጉሥ ነው፥ ኋላም ደግሞ የሳሌም ንጉሥ ማለት የሰላም ንጉሥ ነው። አባትና እናት የትውልድም ቍጥር የሉትም፥ ለዘመኑም ጥንት ለሕይወቱም ፍጻሜ የለውም፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ልጅ ተመስሎ ለዘላለም ካህን ሆኖ ይኖራል” ይላል (ዕብ. 7፥2-3)። ይሁን እንጂ አንዳንድ ጊዜ መልከ ጼዴቅ ኢትዮጵያዊ ነው የሚሉ ሰዎች ያጋጥማሉ። እውን መልከ ጼዴቅ ኢትዮጵያዊ ነውን? ኢትዮጵያዊ ለመሆኑስ ምን ማስረጃ አለ?

መልስ፥ ከነቅዐ ጥበብ፥ ጠያቂአችን በቅድሚያ ስለ ጥያቄዎ እናመሰግናለን። በመልከ ጼዴቅ ማንነትና ዜግነት ላይ የሚነሣው ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እርሱ ከተናገረው ወጣ ያለና ስለ እርሱ ማንነት የተናገረበትን ዐላማ የሳተ ሆኖ ይታያል። እርስዎ እንዳሉት “መልከ ጼዴቅ ኢትዮጵያዊ ነው” ብለው በድፍረት የሚናገሩና የጻፉም ሰዎች አሉ። ይህን ኢመጽሐፍ ቅዱሳዊ አመለካከት፥ በጽሑፍ ካሰፈሩ ሰዎች መካከል ሊቀ ጠበብት አያሌው ታምሩ አንዱና ዋናው ናቸው ማለት ይቻላል። “የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕግጋት” በተሰኘው መጽሐፋቸው ስለ ክህነት በተናገሩበት ክፍል፥ በኦሪት ክህነት ከመሰጠቱ በፊት “ከእግዚአብሔር ተመርጦ የተላከው በታማኝ ሽማግሌ በሴም አማካይነት ከእግዚአብሔር የተሾመው ኢትዮጵያዊው መልከ ጼዴቅ ነው” ብለዋል። አክለውም “የመልከ ጼዴቅ ኢትዮጵያዊነቱ ከነገደ ካም በመወለዱ በስም አጠራሩ በኑሮ ድርጅቱ ይታወቃል” ሲሉ ሦስት “ማስረጃዎችን” ጽፈዋል። አያይዘውም ሐዋርያው ጳውሎስ መልከ ጼዴቅ ከሰው መወለዱ እየታወቀ አባትና እናት የሉትም፤ ዘመኑም አይቈጠርም፤ የተወለደበት፥ የሞተበት አይታወቅም ሲል የዘጋው የመልከ ጼዴቅን ሰውነት ረስቶ ወይም ተሳስቶ ሳይሆን መልእክቱ የተጻፈላቸው ዕብራውያን አንቀበልም ብለው እልክ እንዳይጋቡና እንዳይሰናከሉ ነው ብለዋል። እርሱ ስውር ቢያደርገውም “ደቀ መዝሙሩ ሐዋርያዊ ቀሌምንጦስ ዘእም ነገዱ ለካም ብሎ ገልጾታል” የሚልና ቀሌምንጦስ መልከ ጼዴቅ ከካም ነገድ መሆኑን መናገሩን ጠቅሰዋል። ይህም የመልከ ጼዴቅ ኢትዮጵያዊነት የተገለጠባቸው ነገሮች ብለው ከዘረዘሯቸው ሦስት “ማስረጃዎች” የመጀመሪያውና ትውልዱን የተመለከተው ነው።