ከነቅዐ ጥበብ
ካለፈው ቀጠለ
በፍሬምናጦስ አገልግሎት ክርስትና
በኢትዮጵያ ፍሬ ማፍራት ጀምሮ እንደ ነበረ ባለፈው ዕትም አንብበን ነበር፡፡ በአዳኝነቱ ኢየሱስ፥ ሰውንና እግዚአብሔርን በአንድ
አካል በማገናኘቱና ለፍጹምና ዘላቂ ኅብረት በማብቃቱ ዐማኑኤል፤ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል በተመሠረተ ኅብረት ላይ
ለሚከናወነው የንጉሥነት፣ የነቢይነትና የክህነት አገልግሎት በመሠየሙ ክርስቶስ የተባለው፥ የእግዚአብሔርና የሰው ልጅ የሆነው
የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል በተሰበከባት በሳባ ኢትዮጵያ መዲና በአክሱም ከተማ “ጽዮን” ወይም “ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊት”
የተባለችው ቤተ ክርስቲያን (ማኅበረ ምእመናን) ተቋቁማ እንደ ነበረ ተመልክቶ የነበረውን እናስታውሳለን፡፡
ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃልም በዕብራ
ይስጡ ኳሃል፥ በግሪክኛው አቅሌስያ ምስጢርና ዘይቤ ሲፈታ ጉባኤ ምእመናንን እንደሚያመለክት ተገልጾ ነበር፡፡ በዚህም መሠረት
ከሁለት ቍጥር ጀምሮ ብዛት ያላቸውን ያቀፈ፥ ከዚያም በላይ በመላው ዓለም የነበሩትን፣ ያሉትንና ገናም የሚኖሩት በክርስቶስ ደም
የተዋጁትን ምእመናን ሁሉ ያቀፈች ለክርስቶስ አካልነት፣ ለክርስቶስ ሙሽሪትነት፣ በእግዚአብሔር ጸጋ የበቃችውን የቦታ ክልል
የማይጋርዳትን፣ ከጾታ፣ ከዕድሜ፣ ከወገን ሁሉ የተጠራችውንና የተመረጠችውን አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደሚገልጽ
አንብበን የነበረውን እናስታውሳለን፡፡