Thursday, October 29, 2020

አለቃ ነቅዐ ጥበብ

Read PDF

የስብከተ ወንጌል ሥራ እጅግ በመዳከሙና ሰው ኹሉ ከወንጌል ይልቅ ሌሎች ወሬዎችን ወደ መስማት በማዘንበሉ፣ ይልቁንም ከክርስቶስ ወንጌል ወደ ልዩ ወንጌል ፈጥኖ እየገባ በመኾኑ፣ እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ማዳን ሳይቀበሉ ብዙዎችም ወደ ዘላለም ሞት እየተነዱ በመኾናቸው ይህ ነገር ግድ ያላቸውና ከመናፍስት አምልኮና ከጠላት ዲያብሎስ አሠራር በክርስቶስ ወንጌል ነጻ በወጣው ቤዛ ኵሉ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮችና ምእመናነ ወንጌል የስብከተ ወንጌልን ሥራ ለማጠናከር አንድ ጉባኤ አዘጋጅተው ነበር። በዚህ ጉባኤ ላይ እንዲያገለግሉ ከተጋበዙት ሊቃውንትና መምህራነ ወንጌል መካከል አለቃ ነቅዐ ጥብበ አንዱ ናቸው። በዚህ ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ትምህርት ከዚህ ቀጥሎ ቀርቧል።

በጉባኤው የመጨረሻ ወይም የማጠቃለያ መርሐግብር ላይ እንዲያገለግሉ የተመደቡት አለቃ ነቅዐ ጥበብ ትምህርታቸውን የመሠረቱበትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 3፥18-20 ያለውን ክፍል አነበቡ፤ ቃሉም እንዲህ የሚል ነው።

“በዚያም ዘመን እንዲህ ብዬ አዘዝኋችሁ፦ አምላካችሁ እግዚአብሔር ይህችን ምድር ርስት አድርጎ ሰጥቶአችኋል፤ መሣሪያችሁን ይዛችሁ እናንተ ዐርበኞች ሁሉ በወንድሞቻችሁ በእስራኤል ልጆች ፊት ትሻገራላችሁ። ነገር ግን እጅግ ከብቶች እንዳሉአችሁ ዐውቃለሁና ሴቶቻችሁና ልጆቻችሁ ከብቶቻችሁም በሰጠኋችሁ ከተሞች ይቀመጣሉ፤ ይኸውም እግዚአብሔር እናንተን እንዳሳረፈ፥ ወንድሞቻችሁን እስኪያሳርፍ ድረስ እነርሱም ደግሞ በዮርዳኖስ ማዶ አምላካችሁ እግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ምድር እስኪወርሱ ድረስ ነው፤ ከዚያም በኋላ እናንተ ኹሉ ወደ ሰጠኋችሁ ርስት ትመለሳላችሁ።” (ዘዳ. 3፥18-20)።