Thursday, March 12, 2020


“ወንሕነሰ  ንሰብክ  ክርስቶስሃ  ዘተሰቅለ”
“እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” (1ቆሮ. 1÷23)

የስብከተ ወንጌል ሥራ ሲታሰብ “መሰበክ ያለበት ማነው?” የሚለው ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው። በየሃይማኖቱ የሚሰበኩ ልዩ ልዩ አማልክትና አዳኞች ይኖራሉ። በክርስትና የሚሰበከው አዳኝ ግን አንድ ብቻ፣ እርሱም ሰው የኾነውና የተሰቀለው አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከእርሱ በቀር የሚሰበክ ሌላ አዳኝ የለም። ከእርሱ በቀር ሌሎችን “አዳኞች” አድርጎ የሚሰብክ ሰማያዊ መልአክም ኾነ ምድራዊ ሰው ቢኖር፣ ያ ልዩ ወንጌል ነውና እርሱ በሐዋርያት ቃል ውጉዝ ነው (ገላ. 1፥6-9)። 

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስ መስቀል ከንቱ  እንዳይኾን ወንጌልን  እሰብክ ዘንድ ልኮኛል፤ የምሰብከውም በቃል ጥበብ ወይም “በሰዎች የንግግር ጥበብ” (ዐመት) አይደለም ይላል (1ቆሮ. 1፥17)። ይህም ወንጌሉ ከመስቀሉ ሥራ ጋር በጥብቅ የተቈራኘ መኾኑን ያስረዳል። የምንሰብከውም ሌላውን ሳይኾን “የተሰቀለውን” ክርስቶስን ነው። የመስቀሉ ቃል ወይም “ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ” የሚለው ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ቢኾንም፣ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኀይል ነውና።

Sunday, March 8, 2020

ማስታወቂያ


ጮራ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ለንባብ ትበቃለች።