Saturday, March 31, 2012

በኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥት ታሪክ

                                                             በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ
PDF:በኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥት ታሪክ

በቊጥር 2 የጮራ ዕትም እንደ ተገለጸው፥ የዕብራይስጡ ብሉይ ኪዳን “ኩሽ” ሲል ከካም ልጆች አንዱ የሆነው የኩሽ ነገድ በባለቤትነት ለሰፈሩባት የመሬት ክልልና ለነዋሪዎችዋ ለራሳቸው የሰጠው ስም እንደ ሆነ አንብበናል። ብሉይ ኪዳንን ወደ ጽርእ የተረጐሙት ሊቃውንት ኩሽ የሚለውን ቃል “ጥቊር” የሚያሰኝ ትርጕም እንዲኖረው “ኢትዮጵያ” በሚለው ጽርኣዊ ቃል መተርጐማቸውን ተረድተናል። ሰባ (ሰብዓ) ሊቃውንት የነገደ ኩሽ ጥቊረት የመጣው በሚኖሩበት ምድረ በዳ ካለው የፀሓይ ሐሩር መሆኑን ለመግለጽ ሲሉ፥ ነዋሪዎቹን ብቻ ሳይሆን መኖሪያ አገራቸውን ጭምር ኢትዮጵያ ማለታቸው፥ እንዲሁም በዕብራይስጡ የምድረ በዳ ትርጕም ያለውን ቃል ኢትዮጵያ እያሉ ወደ ጽርእ መመለሳቸው ለቃሉ የነበራቸውን ፅንሰ ሐሳብ እንደሚያመለክት የተሰጠውን ግምገማ ተረድተናል።

ከዚህም በመነሣትና በማያያዝ ኢትዮጵያ፥ የዛሬዪቱ ሱዳን (የቀድሞዪቱ ኑብያ) እና ግብጽ እርስ-በርስ የተገዛዙበት ጊዜ መኖሩን ከግምት በማስገባት፥
አንደኛ ለስሙ በዋና ባለቤትነት የምትታወቀው የዛሬዪቱ ኢትዮጵያ፥
ሁለተኛ በዐረብኛ ጥቊር የማለትን ትርጕም የያዘችው ሱዳን (የቀድሞ ኑብያ-ኢትዮጵያ)፥
ሦስተኛ የኩሽ ወንድም የሚጽራይም አገር የሆነችው ምስር (ግብጽ)፥

በወልም ሆነ በየግል ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ሲጠሩበት እንደ ነበረ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቂት ጥቅሶችን በየተስማሚ ክፍሉ ማንበባችንን እናስታውሳለን።

Tuesday, March 20, 2012

መሠረተ እምነት

በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ
(ካለፈው የቀጠለ)

በአንድ ይሆዋ ከሁለት በላይ የሆኑ አካላት እንዳሉ የሚገልጹትን ጥቅሶች ከመጽሐፍ ቅዱስ ያውም ከብሉይ ኪዳን የመጀመሪው መጽሐፍ አንድ ባንድ መመልከታችንን እናስታውሳለን፡፡ በዚሁ ሁኔታ ጥናታችንን በመቀጠል የብሉይ ኪዳን አባቶች ይሆዋ በአካል ከሦስት እንደማይበልጥና እንደማያንስ አረጋግጠው እንደ ነበረ የዛሬው ዕትም ያስነብበናል፡፡

ነጥብ (ጭብጥ) ሁለት

በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ አባቶች ይሆዋ በአካል ሦስት መሆኑን ተምረው አስተምረዋል፡፡


Monday, March 12, 2012

አለቃ ነቅዐ ጥበብና ቤተሰባቸው

 Read PDF
በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ
ጭውውት
አለቃ ነቅዐ ጥበብና ቤተሰባቸው


ከቊርስ በኋላ፥ ጊዜው በግምት ሦስት ሰዓት ይሆናል፡፡
“እነዚህ ልጆች ዛሬም ወደ ዕርሻ ሄደው አይሠሩም ማለት ነው?” አሉ ወይዘሮ ትደነቂያለሽ ጦቢያው፡፡
“ነገ ይሰማራሉ፤ ዛሬ እኔ የትም ስለማልሄድ እነርሱም እቤት ውለው ቢያጠኑ ይሻላል፡፡” አሉ አለቃ ነቅዐ ጥበብ የምሩ፡፡ ወዲያውም በማከታተል ተጣሩ፡፡ “ግሩም፣ አንተነህ፣ ልዕልት!” አሉ፡፡

“አቤት፥ አቤት!” አሉ፥ ሁሉም በየተራ፡፡

“ኑ፥ ወንበራችሁን ዘርጉና ቀጽሉ፡፡ እስካሁን ምን እየሠራችሁ ነው?” በጥያቄ የተዘጋ፥ ግን መልስ የማይሻ ኮስታራ ትእዛዝ ነበረ፡፡
እነግሩም እየተቻኰሉ ወደ አባታቸው ሲሄዱ፥

“የወንዶቹስ ይሁን፥ መቼም አሁን የሴቷ ልጅ ትምህርት ምን ይባላል? ዳዊት ከደገመች መቼ አነሳትና ነው፤ አትቀድስ፥ አትሠልስ፤ መጣፍ፥ ቅኔ እያሉ ሥራ እሚያስፈቷት፡፡” አጒረመረሙ ወይዘሮ ትደነቂያለሽ፡፡ ልጆቻቸው እንጂ አለቃ የባለቤታቸውን ንግግር አልሰሙትም፤ ቢሰሙትም አይመልሱላቸው እንደ ነበረ ከልማድ የታወቀ ነው፡፡

ሦስቱም ልጆች መጣፍ መጣፋቸውን ይዘው ተቀመጡ፡፡ እግዚአብሔር ትምህርቱን እንዲባርክላቸው አለቃ ጸሎት
አደረሱ፡፡

Tuesday, March 6, 2012

የመዳን ትምህርት

Read PDF
ጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ

የመዳን ትምህርት

“እኔ ጐስቋላ ሰው ነኝ … ማን ያድነኛል? ሮሜ 7፥24 ካለፈው የቀጠለ፡፡

እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ሲመለከት ጻድቅ የሆነ አንድ ሰው ስንኳ ከመካከላችን እንዳልተገኘ ኀጢአት፥ ያልተመረተበት የሰውነት ክፍልም በእያንዳንዳችን እንደ ሌለ የሚገልጹትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ባለፈው ዕትም ተመልክተናል (መዝ. 13፥1-3)፡፡

የዛሬው ዕትም ደግሞ ሰው መበላሸት ከመፈጠሩ ጀምሮ እንዳልሆነ ያስነብበናል፡፡