Monday, January 16, 2017

“ዘቦቱ መርዓት መርዓዊ ውእቱ - ሙሽራዪቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው” (ዮሐ. 3፥29)

መጥምቁ ዮሐንስ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎት መንገድ ጠራጊ፣ ዐዋጅ ነጋሪ እንደ መኾኑ፣ ሕዝቡ፣ ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፣ ከገቢረ ኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ እንዲመለሱና ለንስሓ የሚገባ ፍሬ እንዲያፈሩ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሓ ግቡ” በማለት በበረሓ እያወጀ ነበር የመጣው። 

የሰሙትም ኀጢአታቸውን እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ በእርሱ እጅ ይጠመቁ ነበር። ዮሐንስ እኔ ጐንበስ ብዬ የጫማውን ማሰሪያ ለመፍታት እንኳ የማልበቃ ነኝ፤ ከእኔ የሚበልጠው ከእኔ በኋላ ይመጣል፤ እኔ በውሃ አጠምቃችኋለሁ፤ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል አለ። ሕዝቡን ከጌታው ጋር ካገናኘ በኋላም ሕዝቡ የጌታ፣ ጌታም የሕዝቡ ብቻ መኾናቸውን ለመግለጽ “ሙሽራዪቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው” ሲል ተናገረ። በዚሁ ዐውድ እርሱ እንደ ሚዜ የሚቈጠርና አገልግሎቱም እዚሁ ድረስ ብቻ መኾኑንና መፈጸሙን ገለጸ። 

ከመጥምቁ ዮሐንስ በኋላ የተነሡት የቃሉ አገልጋዮች ሐዋርያትም፣ በዮሐንስ መንገድ ጠራጊነት የመጣውንና ስለ በጎቹ ራሱን አሳልፎ የሰጠውን ጌታ እርሱ ለሞተላቸው ኹሉ በማስተዋወቅ ሙሽራውንና ሙሽራዪቱን የማገናኘት ተግባር ነው የፈጸሙት። ቅዱስ ጳውሎስ “እስመ ፈኃርኩክሙ ለአሐዱ ምት ድንግል ወንጹሕ ክርስቶስ ከመ አቅርብክሙ ኀቤሁ - እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ ዐጭቻችኋለሁ” (2ቆሮ. 11፥2) ሲል የሰጠው ምስክርነትም ይህንኑ እውነት ያስረዳል። 

Monday, January 2, 2017

 መንፈሳዊ መጽሔት ቍጥር 48 ለንባብ በቅታለች

በዚህ ዕትም፦
·        በዘመን ምስክር ዐምድ፦ የብፁዕ አቡነ ዮሐንስን ታሪክ ያስቃኛል።
·        በዕቅበተ እምነት ዐምድ፦ ለመድሎተ ጽድቅ የተሰጠውን ምላሽ ቀጣይ ክፍል ይዟል።
·        በአለቃ ነቅዐ ጥበብ ዐምድ፦ ስግደትን የተመለከተ ትረካዊ ጽሑፍ ቀርቧል።
·       በፍካሬ መጻሕፍት ዐምድ፦ የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እግዚአብሔርም የሚያድናቸውን አዳኝ፥ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ ጎቶንያልን አስነሣላቸው” (መሳፍንት 39) የሚለውን እየተጠቀሰ፥ ቅዱሳን በነገረ ድኅነት ውስጥ ሱታፌ /ተሳትፎ/ አላቸው በማለት ለሚነዛው ኑፋቄ ዐውዳዊ ፍቺ በመስጠት ጥቀሱን ያብራራል።
·        በመንፈሳውያን ቃላት ዐምድ፦ “ሕግ” የተሰኘው ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር የተብራራበትን ጽሑፍ ይዟል።
·        በምስባክ ዐምድ፦  “ተስፋ አለ” በሚል ርእስ ስብከተ ወንጌል ቀርቧል። እና ሌሎችም

አገልግሎቱን ለመደገፍ ቢያስቡ፡- በሚከተለው አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ
ማኅበረ በኵር ስ.ቊ. 0118950459/0911971167
የፖ.ሳ.ቊ. 23956 ኮድ 1000
የባንክ ሒሳብ ቊጥር ማኅበረ በኵር፡-
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ልደታ ቅርንጫፍ
ሒሳብ ቊጥር 1000002276848

ዳሸን ባንክ መገናኛ ቅርንጫፍ
ሒሳብ ቊጥር 0025663937001

አቢሲኒያ ባንክ 6 ኪሎ ቅርንጫፍ
ሒሳብ ቊጥር 1118382

ብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ
ሒሳብ ቊጥር 1600160009836