Sunday, January 15, 2023

አለቃ ነቅዐ ጥበብ

READPDF

(ሐምሌ ወር 2002 ዓ.ም. ታትሞ በወጣው ጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቍጥር 39፥ በአለቃ ነቅዐ ጥበብ ዐምድ ውስጥ የቀረበው ትረካ ማጠንጠኛ የነበረው ሐሳብ “ያለ ወላዲተ አምላክ አማላጅነት ዓለም አይድንም” የሚለው ኢመጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ ነበር። ከሰሞኑ ይህን ጥቅስ አስመልክቶ መምህር ያረጋል አበጋዝ፥ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ያልኾነ ወፍዘራሽ ትምህርት መኾኑን ገልጦ ሲናገር ከማኅበራዊ ሚዲያ አድምጠናል። የስሕተት ትምህርቱ በርሱም ዘንድ ስሕተትነቱ በመገለጡ፥ እውነት ፍሬ ማፍራቱን እንድንረዳና ጌታን እንድናመሰግን ምክንያት ኾኖኗል። ከዛሬ 13 ዓመት በፊት የወጣውን ዘለግ ያለ ጽሑፍ እንድታነብቡት ጋብዘናል።)

ትረካ

በቅርቡ ወደ ርእሰ ሕይወት መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የጕዞ መርሐ ግብር ተዘጋጅቶ ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ለብዙ ዓመታት በተከፈለ መንፈሳዊ ተጋድሎ ከተለያዩ የስሕተት ትምህርቶችና ከመናፍስት አሠራሮች ነጻ የወጣና ምንም ያልተቀላቀለበት ንጹሕ ወንጌል የሚሰበክበት፣ ያልተቀያየጠ አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈጸምበት ደብር ነው፡፡ ደብሩን የሚያውቁት በዚያ ያሉ ወንድሞችንና እኅቶችን ለመጐብኘትና ከእነርሱ ጋር መንፈሳዊ ነገርን ለመከፋፈል÷ ዝናውን የሰሙት ደግሞ የተባለው እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ የጕዞው እድምተኞች ሆነዋል፡፡

አለቃ ነቅዐ ጥበብና ከደቀ መዛሙርቶቻቸው ጥቂቶች÷ እንዲሁም ወደ ስፍራው ለመሄድ የተዘጋጁ ሌሎች ወገኖችም ማልደው በስፍራው ተገኝተዋል፡፡ ወደሚጓዙበት አውቶቡስ ከገቡ በኋላ ጕዞ ከመጀመሩ በፊት÷ ቀሲስ ፍሬ ጽድቅ ጕዟቸውን ለታመነው ፈጣሪ ለእግዚአብሔር በጸሎት ዐደራ ሰጡና ጕዞው ቀጠለ፡፡

Monday, November 14, 2022

ዐዲስ መጽሐፍ በቅርብ ቀን

ብዙ የተደከመበትና "ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ እና አባ እስጢፋኖስ፦ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ" የተሠኘው መጽሐፍ የመጀመሪያ ዕትም ለማኅበረ በኵር የወንጌል አገልግሎት የተሰጠ በመኾኑ፥ የሚታተመው በማኅበረ በኵር በኩል ነው። ይኹን እንጂ የኅትመት ዋጋ ከሚጠበቀው በላይ ስለ ናረ መጽሐፉን ለማሳተም የእናንተ ድጋፍ ያስፈልጋል። ለኅትመቱ ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ በሚከተሉት የማኅበሩ ሒሳብ ቍጥሮች መጠቀም ትችላላችኹ።

ማኅበረ በኵር፦
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000002276848
ብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ 1600160009836
ዳሸን ባንክ 0025663937001
ልዑል እግዚአብሔር ይባርካችኹ



Thursday, October 29, 2020

አለቃ ነቅዐ ጥበብ

Read PDF

የስብከተ ወንጌል ሥራ እጅግ በመዳከሙና ሰው ኹሉ ከወንጌል ይልቅ ሌሎች ወሬዎችን ወደ መስማት በማዘንበሉ፣ ይልቁንም ከክርስቶስ ወንጌል ወደ ልዩ ወንጌል ፈጥኖ እየገባ በመኾኑ፣ እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ማዳን ሳይቀበሉ ብዙዎችም ወደ ዘላለም ሞት እየተነዱ በመኾናቸው ይህ ነገር ግድ ያላቸውና ከመናፍስት አምልኮና ከጠላት ዲያብሎስ አሠራር በክርስቶስ ወንጌል ነጻ በወጣው ቤዛ ኵሉ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮችና ምእመናነ ወንጌል የስብከተ ወንጌልን ሥራ ለማጠናከር አንድ ጉባኤ አዘጋጅተው ነበር። በዚህ ጉባኤ ላይ እንዲያገለግሉ ከተጋበዙት ሊቃውንትና መምህራነ ወንጌል መካከል አለቃ ነቅዐ ጥብበ አንዱ ናቸው። በዚህ ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ትምህርት ከዚህ ቀጥሎ ቀርቧል።

በጉባኤው የመጨረሻ ወይም የማጠቃለያ መርሐግብር ላይ እንዲያገለግሉ የተመደቡት አለቃ ነቅዐ ጥበብ ትምህርታቸውን የመሠረቱበትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 3፥18-20 ያለውን ክፍል አነበቡ፤ ቃሉም እንዲህ የሚል ነው።

“በዚያም ዘመን እንዲህ ብዬ አዘዝኋችሁ፦ አምላካችሁ እግዚአብሔር ይህችን ምድር ርስት አድርጎ ሰጥቶአችኋል፤ መሣሪያችሁን ይዛችሁ እናንተ ዐርበኞች ሁሉ በወንድሞቻችሁ በእስራኤል ልጆች ፊት ትሻገራላችሁ። ነገር ግን እጅግ ከብቶች እንዳሉአችሁ ዐውቃለሁና ሴቶቻችሁና ልጆቻችሁ ከብቶቻችሁም በሰጠኋችሁ ከተሞች ይቀመጣሉ፤ ይኸውም እግዚአብሔር እናንተን እንዳሳረፈ፥ ወንድሞቻችሁን እስኪያሳርፍ ድረስ እነርሱም ደግሞ በዮርዳኖስ ማዶ አምላካችሁ እግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ምድር እስኪወርሱ ድረስ ነው፤ ከዚያም በኋላ እናንተ ኹሉ ወደ ሰጠኋችሁ ርስት ትመለሳላችሁ።” (ዘዳ. 3፥18-20)።

Sunday, April 26, 2020

ዕቅበተ እምነት


መድሎተ ጽድቅ በመድሎተ ጽድቅ ሲመዘን
ክፍል ዐምስት
“መድሎተ ጽድቅ” ለተሰኘውና እንደ ስሙ ኾኖ ላልተገኘው መጽሐፍ ባለፉት አራት ተከታታይ ዕትሞች ምላሽ እየሰጠን መቈየታችን ይታወቃል። በዚህ ዕትምም ምላሽ መስጠታችንን እንቀጥላለን። መጽሐፉ ባሰፈረው ቅደም ተከተል መሠረት የዚህ ዕትም ምላሽ በዋናነት በእኛ ጽሑፎች ላይ ለቀረበው ትችት የተሰጠ ምላሽ ሳይኾን፣ አጠቃላይ ነገር ላይ በማተኰር ጸሓፊው መርሕ ብሎ ላሰፈረው፣ ከመጥቀስ ባለፈ እርሱ ግን ለማይመራበት ጽሑፍ ምላሽ እንሰጣለን።
በ“መድሎተ ጽድቅ” ገጽ 46 ላይ «1.2 መኃትወ ታሪክ ዘመናፍቃን» በሚለው ዐቢይ ርእስ ሥር በሚገኘው «1.2.1.1 ሃይማኖት ምንድነው?» በሚለው ንኡስ ርእስ ሥር ስለ ሃይማኖት ምንነት በቀረበው ሐተታ ውስጥ የተነሡ አንዳንድ ነጥቦችን እንመለከታለን። በመጀመሪያ የምንመለከተው፣ “እግዚአብሔር ሃይማኖትን ሰጠ እኛ ደግሞ ተቀበልን። የሰው ልጅ ሃይማኖትን ይቀበላል እንጂ ሃይማኖትን ሊሠራ ወይም ሊያሻሽል አይችልም። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት’ በማለት የገለጸው ይህን ነው። ዮሐ. 17፥8 እንዲሁም ‘ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው’ ያለው ለዚህ ነው። ስሙንም ማንነቱንም ሊገባን በሚችለው መጠን የገለጠልን ራሱ እግዚአብሔር ነው እንጂ ሃይማኖት የሰው ልጅ በምርምር የደረሰበት አይደለም። ዮሐ. 17፥6።

Thursday, March 12, 2020


“ወንሕነሰ  ንሰብክ  ክርስቶስሃ  ዘተሰቅለ”
“እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” (1ቆሮ. 1÷23)

የስብከተ ወንጌል ሥራ ሲታሰብ “መሰበክ ያለበት ማነው?” የሚለው ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው። በየሃይማኖቱ የሚሰበኩ ልዩ ልዩ አማልክትና አዳኞች ይኖራሉ። በክርስትና የሚሰበከው አዳኝ ግን አንድ ብቻ፣ እርሱም ሰው የኾነውና የተሰቀለው አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከእርሱ በቀር የሚሰበክ ሌላ አዳኝ የለም። ከእርሱ በቀር ሌሎችን “አዳኞች” አድርጎ የሚሰብክ ሰማያዊ መልአክም ኾነ ምድራዊ ሰው ቢኖር፣ ያ ልዩ ወንጌል ነውና እርሱ በሐዋርያት ቃል ውጉዝ ነው (ገላ. 1፥6-9)። 

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስ መስቀል ከንቱ  እንዳይኾን ወንጌልን  እሰብክ ዘንድ ልኮኛል፤ የምሰብከውም በቃል ጥበብ ወይም “በሰዎች የንግግር ጥበብ” (ዐመት) አይደለም ይላል (1ቆሮ. 1፥17)። ይህም ወንጌሉ ከመስቀሉ ሥራ ጋር በጥብቅ የተቈራኘ መኾኑን ያስረዳል። የምንሰብከውም ሌላውን ሳይኾን “የተሰቀለውን” ክርስቶስን ነው። የመስቀሉ ቃል ወይም “ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ” የሚለው ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ቢኾንም፣ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኀይል ነውና።

Sunday, March 8, 2020

ማስታወቂያ


ጮራ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ለንባብ ትበቃለች።

Monday, January 27, 2020

ከዓለመ መጻሕፍት


ሃይማኖተ አበው ቀደምት
ካለፈው የቀጠለ

ነገረ ክርስቶስን በምልአት አብራርተዋል
ክርስትና በፍሬምናጦስ አማካይነት በኢትዮጵያ ከተሰበከበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዐፄ ሱስንዮስ ዘመን ድረስ የነበረው የተዋሕዶ ባህለ ትምህርትቃልና ሥጋ በተዋሕዶ ወልድ ዋሕድ አካል ልጅ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው። በተዓቅቦ ባሕርያት ግብራት የባሕርይ ልደታት ወልደ አብ በመለኮቱ (በመለኮቱ የአብ ልጅ) ወልደ ማርያም በትስብእቱ (በሰውነቱ የማርያም ልጅ) አብ ቀባዒ (ቀቢ) ወልድ ተቀባዒ (ተቀቢ) መንፈስ ቅዱስ ቅብ (ቅብዐት) ሥግው ቃል (ሥጋ የኾነው ቃል) በተዋሕዶ ገንዘብ ባደረገው በሥጋ ርስት በሥጋ ባሕርይ መንፈስ ቅዱስን ከአብ ተቀበሎ ተቀብቶ፥ በቅባት መሲሕ ወበኵር (መሲሕና በኵር) በኵረ ልደት ለኵሉ ፍጥረት (ከምእመናን ኹሉ በጸጋ ልጅነት የመጀመሪያ ልጅ) ዳግማይ አዳም (ኋለኛው አዳም) ንጉሠ ነገሥት ሊቀ ካህናት፤ ነቢይ ሐዋርያ፣ ላእክ መልአክ (አገልጋይ መልእከተኛ) ኾነ ወይም ተባለ ማለት ነው።ይላሉ።ይህ ኹሉ በቅባት የሚሰጥ የሹመትና የግብር ስምሲኾን ከመቀባቱ ጋር ተያይዞ መሲሕነቱን አምልቶ አስፍቶ አጕልቶ የሚያሳይ ነው።

ባህለ ትምህርታቸው ተዋሕዶ ኾኖ ሳለ በካሮችና ቅብዐቶች ስማቸው ተቀምቶየጸጋ ልጆችአንዳንድ ጊዜምሦስት ልደትየተሰኙት ለክርስቶስ ኹለት የባሕርይ ልደታት፣ አንድ የግብር ልደት በድምሩ ሦስት ልደታት አሉት ብለው ስለሚያምኑና ስለሚያስተምሩ ነው። ኹለቱ የባሕርይ ልደታት የሚባሉትም ወልድ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት የተወለደው ልደትና ድኅረ ዓለም ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት የተወለደው ልደት ነው። ስለዚህ ወልድበአምላክነቱ የአብ የባሕርይ ልጅ፥ በሰውነቱ የማርያም የባሕርይ ልጅ፥ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰብእ፥ ወልድ ዋሕድነው። በመጀመሪያው ልደት ወልድ የአብ የባሕርይ ልጅ ነው፤ለአብ ወልድ ዘበአማን (የባሕርይ ልጅ) በሚባልበት በአባቱ ባሕርይ ለማርያም ወልድ ዘበአማን (የባሕርይ ልጅ) አይባልም፤ ጌታዋ ፈጣሪዋ እንጂ። እንደዚሁ ደግሞ ለማርያም ወልድ ዘበአማን በሚባልበት በናቱ ባሕርይ ለአብ ወልድ ዘበአማን አይባልም፤ ዘበጸጋ (የጸጋ ልጅ) እንጂ።ይላሉ።

Wednesday, October 16, 2019

ከዓለመ መጻሕፍት


ሃይማኖተ አበው ቀደምት

“ሃይማኖተ አበው ቀደምት” የተሰኘውና በቁም ጽሑፍ ተዘጋጅቶ የተባዛው መጽሐፍ፣ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ (ኪ.ወ.ክ.) ጽፈውት ለአቶ ደስታ ተክለ ወልድ በዐደራ የሰጡትና በዶ/ር ብርሃኑ አበበ አማካይነት ምዕራብ ጀርመን ፍራንክፈርት በሚገኘው በፍሬቤንዩስ ድርጅት የታተመ መኾኑን በመጽሐፉ ላይ ደስታ ተክለ ወልድ የሰጡት መግለጫ ያስረዳል። መጽሐፉ ምንም እንኳ በቤተ ክህነት ዐማርኛ በመምህራን ቋንቋ የተጻፈ መኾኑን ስለሚገልጥ፣ አንዳንድ ታሪኮችና ጸሎቶችም በግእዝ በመቅረባቸው በቀላሉ ለመረዳት አስቸጋሪ ቢኾንም፣ ከ15 የሚበልጥ ብዙ ዐይነት ምዕላድ በማየትና በመመልከት፣ በማስተዋልና በመመርመር፣ በማነጻጸርም የተዘጋጀ በመኾኑ ከፍ ያለ ግምት የሚሰጠው ሥራ ነው። 

በውስጡም የሦስቱን ማለትም የተዋሕዶን፣ የካራንና የቅባትን ባህላተ ትምህርት ምንነት ይዟል። በዘመናቸው የትምህርት ሕጸጽና የሃይማኖት ጕድለት፣ መከራና ስደት፣ ጠብና ክርክር ከዚሁ ጋር ተያይዞ በባህለ ሃይማኖት ልዩነት ምክንያት ምላስና ዐንገት እስከ መቍረጥ የደረሰ አሳዛኝ ቅጣት የፈጸሙ ነገሥታትና የኢትዮጵያ ግብጻውያን ጳጳሳት ታሪክም የተካተተበት መኾኑን መጽሐፉ ይገልጣል።

Saturday, August 31, 2019

የዘመን ምስክር

READ PDF

አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
ካለፈው የቀጠለ
መዝገበ ቃላት
ኪ.ወ.ክ. ሲነሡ ከስማቸው ጋር ተያይዞ በዋናነት የሚነሣው ዕውቅ ሥራቸው “መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ” ነው። የዚህ ንባቡ በግእዝ፣ ፍቺው በዐማርኛ የኾነ መዝገበ ቃላት ሥራ ጀማሪ በእርሳቸው ብርዕ፣ “በሮማውያን ዘንድ የከበሩ ትምህርት ከጥፈት ያስተባበሩ፥ በትምርታቸውም የተደነቁና የታወቁ፥ በሀገራቸው ግን እንደ ነቢያት የተናቁ እንደ ሐዋርያት የተጠቁ፥ እንደ ዮሴፍም ወንድሞቻቸው ጠልተው ተመቅኝተው ለማይረባ ዋጋ የሸጧቸው የአንኮበሩ ሊቅ” በማለት የተገለጡት መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ወልደ አባ ተክሌ ሲኾኑ፣ ፈጻሚው ደግሞ ኪ.ወ.ክ. መኾናቸው በመጽሐፉ ላይ ተጠቅሷል።

“ሥራን መንቀፍ በሥራ ነው እንጂ በቃል ብቻ መንቀፍ አይበቃም” የሚል ዐቋም የነበራቸው መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ይህን የግስ (የመዝገበ ቃላት) መጽሐፍ ለማዘጋጀት የተነሣሡት፣ ዲልማን የተባለው የውጭ አገር ሊቅ ያዘጋጀውን የግእዝ ግስ ከተመለከቱ በኋላ፣ በተለይ በሞክሼ ፊደላት (ሀሐኀ፣ ዐአ፣ ሠሰ እና ጸፀ) አጠቃቀም ላይ የታየውን ጕድለት በሥራቸው ለመንቀፍ (ትክክለኛውን ለማሳየት) ነው። ኾኖም ዲልማን የውጭ ዜጋ ኾኖ ግእዝን አጥንቶ መዝገበ ቃላት በማዘጋጀቱ ከፍ ያለ አክብሮትና አድናቆት እንደ ቸሩትም በመዝገበ ቃላታቸው ውስጥ እናነባለን። ሞክሼዎቹ ፊደላት እንደ ቀድሞው የድምፅ ልዩነት ባይኖራቸውም የመልክ ልዩነት ስላላቸውና ምስጢራቸውና ስማቸውም እንደ መልካቸው የተለያየ ስለ ኾነ ያ ተጠብቆ መጻፍ አለበት ይላሉ።

Thursday, August 29, 2019

የዘመን ምስክር


አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
መግቢያ
በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በተለይ የነገረ ሃይማኖት፣ የቋንቋና ሥነ ጽሑፍ፣ የባሕረ ሐሳብም (የዘመን ቍጥር) ጉዳይ ሲነሣ በጕልሕ ከሚጠቀሱት ሊቃውንት መካከል፣ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ግንባር ቀደም ናቸው። አንዳንዶች ስማቸውን በአኅጽሮት (ባጭሩ) ኪ.ወ.ክ. እያሉ ይጠራሉ። እኒህ የነገረ መለኮት፣ የሰዋስውና የመዝገበ ቃላት ሊቅ በዋናነት ነገረ ክርስቶስን አስመልክቶ በሚከተሉትና በኢትዮጵያ ቀዳሚው ኦርቶዶክሳዊ ባህለ ትምህርት በኾነውና ተቃዋሚዎቹ “ሦስት ልደት” (ጸጋ) እያሉ በሚጠሩት ባህለ ትምህርት ምክንያት በሥልጣን ላይ ያለው ቡድን በአንዳንድ ሥራዎቻቸው እየተጠቀመ ስማቸውን ግን በተገቢው መንገድ ለማንሣትና ተገቢውን ስፍራ ለመስጠት ቢቸገርም፣ ሊቅነታቸውን ግን በምንም መንገድ ሊያስተባብል አይችልም።

አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ከነገረ ክርስቶስ በተጨማሪ በአንዳንድ አስተምህሮቶችና ታሪኮች ላይም ለየት ያሉና አነጋጋሪ የሆኑ ጉዳዮችን በድፍረት ያቀርባሉ። ከዚህ የተነሣ እርሳቸውን ለማጣጣል የሚሞክሩ አንዳንድ ደፋሮች ባይጠፉም፣ እውነትን ደፍረው በመናገራቸውና እውነትን ይዘው ለብቻቸውም ቢኾን በመቆማቸው ተከታዮችና ደጋፊዎችን አላጡም። ስለ እርሳቸው ሊነገርና ሊጻፍ የሚገባው ብዙ ነገር ቢኖርም ጥቂቱንም እንኳ እንጻፍ ብንል ብዙ ይኾናል። በዚህ ጽሑፍ የገጠመንም ይኸው ነው። ለመኾኑ እኒህ ሊቅ ማናቸው? ሥራዎቻቸውስ የትኞቹ ናቸው? ለአገርና ለቤተ ክርስቲያን መታደስ ምን አበረከቱ? የሚሉትንና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ቀጥሎ እንቃኛለን።