Saturday, December 31, 2011

ሰላማችን ክርስቶስ ነው

Read PDF
(በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ)
ዓለም ዛሬ በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት በታላቅ ሥጋት ላይ ወድቃ ትሸበራለች፡፡ ድርቅና በረሓማነት የዓለምን ሕዝብ ለረኃብና ለበሽታ አጋልጦታል፡፡ ከዓለም ሕዝብ ከፊሉ ያህል በጐርፍ በረኃብ፥ በበሽታ፥  በመሬት መንቀጥቀጥና በዐውሎ ነፋስ ሕይወቱንና ንብረቱን እያጣ ነው፡፡

ይህም ብቻ አይደለም፤ አንዱ መንግሥት ከሌላው በፖለቲካ፣ በድንበር እየተናቈረ፥ በንግድ ውድድር እየተጐናተለ፥ ጕልበተኛው መንግሥት ደካማውን እያጠቃ ነው፡፡ እንዲያውም የአንዳንድ አገር ሕዝብ እርስ በርሱ በጦርነት ሲተላለቅ ይታያል፡፡ ስለዚህም ነው “ሰላም! ሰላም!” የሚል ድምፅ በዓለማችን ዙሪያ በከፍተኛ ሁኔታ የሚስተጋባው፡፡

Thursday, December 15, 2011

ትዳር ለመመሥረት መሠረታዊ ጉዳዮች


                                   Read PDF                  
    በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 1፣ ላይ  የቀረበ
ወንዶች ወይም ሴቶች ትዳር ለመያዝ ሲፈልጉ በዕድሜ ለአካለ መጠን መድረስ አለባቸው፡፡ ሥጋዊ እድገት ብቻ ሳይሆን በመንፈስም መጐልመስና በአእምሮም መብሰል አስፈላጊ ነው፡፡
ለአካለ መጠን መድረሳችንን እንዴት ማወቅ እንችላለን? ለአካለ መጠን መድረሳችንን ማወቅ የምንችለው ከዚህ በታች የተጻፉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ስንችል ነው፡፡

በውሳኔዬ ለመጽናት እችላለሁን?

Saturday, December 10, 2011

“እኔ ጐስቋላ ሰው ነኝ . . . ማን ያድነኛል?”

Read PDF 
“እኔ ጐስቋላ ሰው ነኝ  . . . ማን ያድነኛል?” ሮሜ 7፥24

ሰው ተፈጥሮ ካመፀበት፥ ተፈጥሮን መቈጣጠር ካቀተው ብዙ መቶ ዓመታት ዐልፈዋል፡፡ የምድር ፍጥረት ሁሉ ለእርሱ ተፈጥሮለት የነበረና ሁሉን ለመቈጣጠርና ለመግዛት በተፈጥሮ ባሕርዩ ባለመብት ተደርጎ የክብርን አክሊል በመቀዳጀት የተሾመ ሰው (ዘፍ. 1፥28፤ መዝ. 8፥3-8) በአሁኑ ጊዜ ሲታይ ከብዙ አቅጣጫዎች ጥቃት የሚደርሰበትና አደጋን የሚፈራ ድንጉጥ ፍጡር ሆኗል (ኢዮ. 7፥1-31)፡፡
በቀላሉ አገላለጽ የፀሓይ ዋዕይ ያጠቃዋልና መጠለያን ይሻል፡፡ በተቃራኒው ሁኔታ ቊር ቢያኮራምተው ሙቀትን ይፈልጋል፡፡ በእሾኽና በእንቅፋት በቀላሉ ስለሚጐዳ ጫማን ለማዘጋጀት ይገደዳል (ዘፍ. 3፥18፤ ኢሳ. 25፥4-5)፡፡

Tuesday, December 6, 2011

በኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥት ታሪክ

Read IN PDF
                                                  በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 1፣ ላይ  የቀረበ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በራሱ መሠረትነት ላይ ያቋቋማትን የእግዚአብሔር መንግሥት (መንግሥተ ሰማያት) እድገት የሚገልጽ ምሳሌ ሲናገር እንዲህ አለ፡፡
        “መንግሥት ሰማያት ሰው ወስዶ በዕርሻ የዘራትን የሰናፍጭ ቅንጣትን ትመስላለች፡፡ እርስዋ ከዘር ሁሉ ታንሳለች ባደገች ጊዜ ግን ከአትክልቶች ሁሉ ትበልጣለች፥ የሰማይ ወፎች መጥተው በቅርንጫፎችዋ የሚሰፍሩባት ዛፍ ትሆናለች” (ማቴ.13፥31-32)፡፡