Friday, November 9, 2012

የመዳን ትምህርት

Read in PDF

                                                            (በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 4 ላይ የቀረበ)

“እኔ ምንኛ ጐስቋላ ሰው ነኝ … ማን ያድነኛል? …” (ሮሜ 7፥24)
ካለፈው የቀጠለ

ባለፈው ዕትም የሰው አፈጣጠር እንከን አልባ እንደ ነበር ከእግዚአብሔር ቃል ማንበባችንን እናስታውሳለን፡፡ ግሩምና ድንቅ ለተባለ የውስጥና የውጭ ውበት ባለቤት ሆኖ የተፈጠረው ሰው፥ “እኔ ምንኛ ጐስቋላ ሰው ነኝ . . . ማን ያድነኛል?” እንዲል ያስገደደው ብልሹነት እንዴትና ከየት መጣበት የሚለው ጥያቄ በዛሬው ዕትም ይመለሳል።

የሰው ተፈጥሮ መበላሸት ከየት መጣ?

          “ሕያው ነፍስ” ያሰኘውን የሕይወት እስትንፋስ ከሕያው አምላክ በመቀበሉ እግዚአብሔርን መስሎና ከማንኛውም ፍጥረት በልጦ እንከን አልባ የሆነው ሰው አንድ ቀን በእባብ እንደ ተጐበኘ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል።