Monday, March 30, 2015

ፍካሬ መጻሕፍት

የእግዚአብሔር ቃል ሳይዛባ በተነገረበት መንፈስ ሊተረጐም ይገባል፡፡ በዚህ ዐምድ ቃሉ በዐውዱ መሠረት ሊተረጐም እንደሚገባ በማስረዳት፥ የተሳሳተ ትርጕም እየተሰጣቸው ያሉ ጥቅሶችን ከመጽሐፍ ቅዱስ ለአብነት በማንሣት የቃሉን ትክክለኛ መልእክት ለማስተላለፍ ጥረት ይደረጋል፡፡

“ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል$ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል፡፡ ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውሃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላችኋለሁ ዋጋው አይጠፋበትም፡፡” (ማቴ 10$41-42)

የእግዚአብሔር ቃል በተጻፈበት ዐውድ መሠረት ሊተረጐም ይገባል፡፡ ቃሉን የሚያነብ ሁሉ በቃሉ ላይ ሳይጨምር፣ ከቃሉም ላይ ሳይቀንስ፣ ወይም ቃሉን በተነገረበት መንፈስ ሳይሆን ለባህሉና ለልማዱ በሚስማማ ስልት እንዳይተረጕመውና በተሳሳተ መንገድ እንዳይረዳው ጥንቃቄ ማድረግ አለበት፡፡ ይሁን እንጂ በብዙዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቃል በዐውዱ መሠረት እየተተረጐመና እየተኖረበት ነው ማለት አያስደፍርም፡፡

Monday, March 2, 2015

የዘመን ምስክር

በዚህ ዐምድ ለቤተ ክርስቲያን መሻሻልና መለወጥ የተጋደሉ፥ ለአገርና ለወገን የሚጠቅም መልካም ሥራን የሠሩ አበውን ሕይወትና የተጋድሎ ታሪክ አሁን ላለውና ለቀጣዩ ትውልድ አርኣያ እንዲሆን እናስተዋውቃለን፡፡

ነጋድረስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ
መግቢያ
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ በኻያኛው ክፍለ ዘመን መባቻ አካባቢ የነበሩ ኢትዮጵያዊ ምሁርና ተራማጅ አስተሳሰብ የነበራቸው ግለ ሰብ ነበሩ፡፡ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ የተወለደው በ1878 ዓ.ም. በአድዋ አቅራቢያ በምትገኝ ማይሚሸም በምትባል መንደር ነው፡፡ የገብረ ሕይወት ባይከዳኝ  አባት ገብረ ሕይወት በተወለደ በዐጭር ጊዜ  ውስጥ ነው የሞቱት፡፡
ገብረ ሕይወት ኤርትራ ውስጥ ምጽዋ አጠገብ ምንኩሉ በተባለ ቦታ በሚገኘው የሲውዲን ሚስዮን (Swedish Mission) ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ጀረጃ ትምህርትን አግኝቶአል፡፡ ምንኩሉ በነበረበት ጊዜ አለቆቹ ከነበሩት መካከል አንዱ ስመ ጥሩ ምሁር አለቃ ታየ ነበሩ፡፡ ከዚህም በመነሣት ይመስላል በኋላ ላይ አለቃ ታየ እና ከንቲባ ገብሩን በተመለከተ የሚከተለውን አስተያየት የሰጠው፡- “ሦስት ዓመት ምሉ አዲስ አበባ ላይ ስቀመጥ እንደነዚህ ሁለት ሰዎች አርጎ መንግሥቱን የሚወድ ሰው አላየሁም፡፡ ይህ ደግነታቸው ግን እስከ ዛሬ ድረስ አልታወቀላቸውም ይመስለኛል፡፡ እጅግ ያሳዝናል፡፡ የነሱን ዕድል ያየ ሰው የኢትዮጽያ መንግሥት ለወዳጁ አይጠቅምም ብሎ ተስፋ ይቈርጣልና።” (ገጽ 15)