Sunday, February 26, 2012

መጽሐፈ ዕዝራ ካልእ

Read PDF
በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ
ካለፈው የቀጠለ
 በም. 1፥3-4 በሞሪያ ተራራ በጽዮን አምባ ላይ ንጉሥ ሰሎሞን ባሠራው ቤተ መቅደስ ውስጥ “የእግዚአብሔር ሕግ ማደሪያ ታቦተ ጽዮን” በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ዘመን እንደ ነበረች ይናገራል፡፡ በአገላለጹ ከዜና መዋዕል ካልእ 35፥3 ጋር ይስማማል፡፡  ጊዜው የኢዮስያስ 18ኛ የግዛት ዓመት ስለ ሆነ (2ዜና. 35፥19) ሰሎሞን ከሞተ 359 ዓመት ዐልፎአል ማለት ነው፡፡

ም. 1፥54-55 ከለዳውያን የእግዚአብሔርን ማደሪያ ታቦት ማርከው ወደ ባቢሎን እንደ ወሰዱ ይናገራል፤ ትረካው ግን፡-
1.      ታቦተ ጽዮን በሰሎሞን ዘመን ተሰርቃ ተወስዳ ነበር ባዮችን የሚደግፍ ሆኖ አልተገኘም፡፡ መሰረቋን ማወቅ ያልቻለ እንደ ዕዝራ ሱቱኤል ያለ ሰው ነው ካልተባለ በቀር፤ ዕዝራ ሱቱኤል 9፥21-22፡፡
2.     የተረፈ ኤርምያስ ጸሓፊ ቤተ መቅደሱ በውስጡ ካለው ዕቃ ጋር ተሰወረ በሚለው ሐሳብ አልተስማማም፤ ተረፈ ኤር. 8፥13፡፡

Wednesday, February 22, 2012

ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ጠቅላላ ዕውቀት

 Read PDF
በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 3 ላይ የቀረበ


ባንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዝ በብሉይ ኪዳን  መጨረሻ ከገጽ 721 እስከ 1037 በሌሎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዞች የማይገኙ መጻሕፍት በመጨመራቸው ተጨንቀውና ግራ ተጋብተው ያውቃሉን? «ተጨማሪ (ዲዩትሮካኖኒካል) የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት» በሚል የክፍል መጠሪያ የተጨመሩት መጻሕፍት ዐሥራ ስምንት ናቸው (በ1980 ዕትም)፡፡

በውሳኔ የተጨመሩት መጻሕፍት የሚገኙበት ጥራዝ ባንዳንድ ሰዎች ዘንድ እንደ ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ ሲቈጠር፥ እነርሱ የሌሉበት ጥራዝ ግን ጐደሎ መጽሐፍ ቅዱስ ተብሎ ሲጠራ ተሰምቷል፡፡

Wednesday, February 15, 2012

ጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 42 ለንባብ በቅቷል፡፡


 REad PDF
ርእሰ አንቀጹ፡-
እውነት ምንድር ነው? በማለት የእውነትን ፍለጋ ተከትለን እውነት ወደሆነውና ወደሚያድነው እውነት ወደ ኢየሱስ ያድርሰናል፡፡
መሠረተ እምነት
ስለ ክርስቶስ መካከለኛነት ራሱ ክርስቶስ ያስተማረውን እውነት ያብራራል፡፡ መካከለኛነቱን ለማስተባብል የሚሰነዘሩ ጕንጭ አልፋ ክርክሮችን ይሟገታል፤ ተከራክሮም በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ይረታል፡፡


ክርስቲያናዊ ምግባር
በማቴ. 5÷10 ላይ ተመሥርቶ ስለጽድቅ የሚደርሰው ስደት ለክርስቲያኖች ያለውን ጥቅም እና በአሳዳጆች ላይ የሚያስከትለውን ጕዳት ይገልጣል፡፡
የዘመን ምስክር
የቀደሙ አባቶቻችን የሠሩትን መልካም ሥራና ያሳዩትን በጎ አርኣያነት የሚዘክረው ይህ ዐምድ ለውጥ ናፋቂውን ብላቴን ጌታ ኅሩይንና መልካም ሥራዎቻቸውን ያስተዋውቃል፡፡   
ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
በቊጥር 94 በስያሜ 81 እየተባለ ስለሚጠራው፣ ከሒሳብ ስሌት ውጪና ግራ አጋቢ ስለሆነው  የመጽሐፍ ቅዱስ አቈጣጠር ለቀረበ ጥያቄ፣  ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ 
66 + 28 = 84 መጻሕፍት፡፡
ወቅታዊ ጕዳይ
ኦርቶዶክስ ማነው? በሚል ርእስ በተከታታይ በሚቀርበው በዚህ ርእስ ማኅበረ ቅዱሳን በአስተምህሮው ኦርቶዶክሳዊ መሆን አለመሆኑን ይፈትሻል፡፡ በዚህ ዕትም አንድ ቀሪ ነጥብ ቢኖርም፣ ማኅበረ ቅዱሳን ለመጽሐፍ ቅዱስ ያለው አመለካከት ተገምግሞ ኦርቶዶክሳዊ አለመሆኑ ተደርሶበታል፡፡ 
ሌሎችም ጽሑፎች ተካተዋል፡፡ በ“እውነት ምንድር ነው?” የጀመረው የዚህ መጽሔት መልእክት “እስከ ማእዜኑ” በተሰኘውና እውነትን በሚያቀነቅነው የዮናስ አድማሱ ግጥም ይደመድማል፡፡
መጽሔቱን በየመንፈሳዊ መዝሙር ቤቶች ያገኙታል፡፡

Wednesday, February 1, 2012

የሰይጣን ባቄላ

Read PDF
የሰይጣን ባቄላ
በጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 2 ላይ የቀረበ


የሳባ ታሪኮች ከሚለው መጽሐፍ የተገኘ (የአንድ ሰባኪ ትረካ)

አንድ ቀን እጅግ ብዙ የሆነ አሳማ አንዱን ሰው ተከትሎ ሲጥመለመል አየሁ፡፡ የአሳማ መንጋ ከወደ ኋላ ሆኖ ሲነዱት እንኳ ግራና ቀኝ እያለ ነጂውን ያስቸግራል:: በዚህ ጊዜ ግን ያለ አንዳች ችግር ተቀጣጥሎ ሰውየውን ይከተል ነበር፡፡ እኔም ሁኔታውን ለመረዳት ተከታትዬ ተመለከትሁ፡፡ ሰውየውም እየመራ ከብት ወደሚታረድበት ቄራ ሲደርስ በሩን ከፍቶ የተከተለውን የአሳማ መንጋ አስገብቶ መልሶ ዘጋ፡፡

እኔም ወደ ሰውየው ቀርቤ ያለአንዳች ችግር ይህን የሚያህል የአሳማ መንጋ ወደ ቄራው ውስጥ ልትመራው እንደ ምን ተቻለህ? ብዬ ብጠይቀው ከት ብሎ ስቆ “በብብቴ የያዝኩትን አንድ ከረጢት ባቄላ አላየህም ይሆናል፡፡ አሳማዎቹ ደስ የሚያሰኛቸውን ነገር ሳንጠባጥብላቸው ወደ መሞቻቸው እንደሚደርሱ ሳያስተውሉ ያንን እየለቃቀሙ ወደሚታረዱበት ቄራ ድንገት ገቡ እንዳይወጡም ዘጋሁባቸው” አለኝ፡፡