Wednesday, February 15, 2012

ጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 42 ለንባብ በቅቷል፡፡


 REad PDF
ርእሰ አንቀጹ፡-
እውነት ምንድር ነው? በማለት የእውነትን ፍለጋ ተከትለን እውነት ወደሆነውና ወደሚያድነው እውነት ወደ ኢየሱስ ያድርሰናል፡፡
መሠረተ እምነት
ስለ ክርስቶስ መካከለኛነት ራሱ ክርስቶስ ያስተማረውን እውነት ያብራራል፡፡ መካከለኛነቱን ለማስተባብል የሚሰነዘሩ ጕንጭ አልፋ ክርክሮችን ይሟገታል፤ ተከራክሮም በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ይረታል፡፡


ክርስቲያናዊ ምግባር
በማቴ. 5÷10 ላይ ተመሥርቶ ስለጽድቅ የሚደርሰው ስደት ለክርስቲያኖች ያለውን ጥቅም እና በአሳዳጆች ላይ የሚያስከትለውን ጕዳት ይገልጣል፡፡
የዘመን ምስክር
የቀደሙ አባቶቻችን የሠሩትን መልካም ሥራና ያሳዩትን በጎ አርኣያነት የሚዘክረው ይህ ዐምድ ለውጥ ናፋቂውን ብላቴን ጌታ ኅሩይንና መልካም ሥራዎቻቸውን ያስተዋውቃል፡፡   
ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
በቊጥር 94 በስያሜ 81 እየተባለ ስለሚጠራው፣ ከሒሳብ ስሌት ውጪና ግራ አጋቢ ስለሆነው  የመጽሐፍ ቅዱስ አቈጣጠር ለቀረበ ጥያቄ፣  ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ 
66 + 28 = 84 መጻሕፍት፡፡
ወቅታዊ ጕዳይ
ኦርቶዶክስ ማነው? በሚል ርእስ በተከታታይ በሚቀርበው በዚህ ርእስ ማኅበረ ቅዱሳን በአስተምህሮው ኦርቶዶክሳዊ መሆን አለመሆኑን ይፈትሻል፡፡ በዚህ ዕትም አንድ ቀሪ ነጥብ ቢኖርም፣ ማኅበረ ቅዱሳን ለመጽሐፍ ቅዱስ ያለው አመለካከት ተገምግሞ ኦርቶዶክሳዊ አለመሆኑ ተደርሶበታል፡፡ 
ሌሎችም ጽሑፎች ተካተዋል፡፡ በ“እውነት ምንድር ነው?” የጀመረው የዚህ መጽሔት መልእክት “እስከ ማእዜኑ” በተሰኘውና እውነትን በሚያቀነቅነው የዮናስ አድማሱ ግጥም ይደመድማል፡፡
መጽሔቱን በየመንፈሳዊ መዝሙር ቤቶች ያገኙታል፡፡

4 comments:

  1. እየሰጣችሁት ላለው ትምህርት ጌታ ይባርካችሁ፡፡

    ReplyDelete
  2. Wegnoch sel maniem behone minem asteyayte atisetu ewnetegna nen kalchehu yerasacheu tsehufe becha tsafu maninem atinkefu hulum ewnet manew ewnets yetu new belo mermero seyawkew wed gebawe godana yehedal yemin mezebark new beka ewnet ena ewnet new yalachehutin becha tsafu manim maninem menkefe yelebetim " berasih ayne weset yalewin gudfe sataweta be wendmihe ayene weset yegebawi gudefe yemitaweta ante maneh" le hulachinem Leule Egzabeher Lebona yeseten ye Ewnet amelak ewnetin yegeltse amen.

    ReplyDelete
  3. corawoch bertulen benante Geta talak negern eyesera new.

    ReplyDelete
  4. I am from Mekelle, how I can I get urs chorra starting from 1up to 24.if possible would you please help me to get urs hard copy or in soft copy in pdf
    Thanks

    ReplyDelete