Thursday, October 29, 2020

አለቃ ነቅዐ ጥበብ

Read PDF

የስብከተ ወንጌል ሥራ እጅግ በመዳከሙና ሰው ኹሉ ከወንጌል ይልቅ ሌሎች ወሬዎችን ወደ መስማት በማዘንበሉ፣ ይልቁንም ከክርስቶስ ወንጌል ወደ ልዩ ወንጌል ፈጥኖ እየገባ በመኾኑ፣ እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ማዳን ሳይቀበሉ ብዙዎችም ወደ ዘላለም ሞት እየተነዱ በመኾናቸው ይህ ነገር ግድ ያላቸውና ከመናፍስት አምልኮና ከጠላት ዲያብሎስ አሠራር በክርስቶስ ወንጌል ነጻ በወጣው ቤዛ ኵሉ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮችና ምእመናነ ወንጌል የስብከተ ወንጌልን ሥራ ለማጠናከር አንድ ጉባኤ አዘጋጅተው ነበር። በዚህ ጉባኤ ላይ እንዲያገለግሉ ከተጋበዙት ሊቃውንትና መምህራነ ወንጌል መካከል አለቃ ነቅዐ ጥብበ አንዱ ናቸው። በዚህ ጉባኤ ላይ ያቀረቡት ትምህርት ከዚህ ቀጥሎ ቀርቧል።

በጉባኤው የመጨረሻ ወይም የማጠቃለያ መርሐግብር ላይ እንዲያገለግሉ የተመደቡት አለቃ ነቅዐ ጥበብ ትምህርታቸውን የመሠረቱበትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 3፥18-20 ያለውን ክፍል አነበቡ፤ ቃሉም እንዲህ የሚል ነው።

“በዚያም ዘመን እንዲህ ብዬ አዘዝኋችሁ፦ አምላካችሁ እግዚአብሔር ይህችን ምድር ርስት አድርጎ ሰጥቶአችኋል፤ መሣሪያችሁን ይዛችሁ እናንተ ዐርበኞች ሁሉ በወንድሞቻችሁ በእስራኤል ልጆች ፊት ትሻገራላችሁ። ነገር ግን እጅግ ከብቶች እንዳሉአችሁ ዐውቃለሁና ሴቶቻችሁና ልጆቻችሁ ከብቶቻችሁም በሰጠኋችሁ ከተሞች ይቀመጣሉ፤ ይኸውም እግዚአብሔር እናንተን እንዳሳረፈ፥ ወንድሞቻችሁን እስኪያሳርፍ ድረስ እነርሱም ደግሞ በዮርዳኖስ ማዶ አምላካችሁ እግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ምድር እስኪወርሱ ድረስ ነው፤ ከዚያም በኋላ እናንተ ኹሉ ወደ ሰጠኋችሁ ርስት ትመለሳላችሁ።” (ዘዳ. 3፥18-20)።

Sunday, April 26, 2020

ዕቅበተ እምነት


መድሎተ ጽድቅ በመድሎተ ጽድቅ ሲመዘን
ክፍል ዐምስት
“መድሎተ ጽድቅ” ለተሰኘውና እንደ ስሙ ኾኖ ላልተገኘው መጽሐፍ ባለፉት አራት ተከታታይ ዕትሞች ምላሽ እየሰጠን መቈየታችን ይታወቃል። በዚህ ዕትምም ምላሽ መስጠታችንን እንቀጥላለን። መጽሐፉ ባሰፈረው ቅደም ተከተል መሠረት የዚህ ዕትም ምላሽ በዋናነት በእኛ ጽሑፎች ላይ ለቀረበው ትችት የተሰጠ ምላሽ ሳይኾን፣ አጠቃላይ ነገር ላይ በማተኰር ጸሓፊው መርሕ ብሎ ላሰፈረው፣ ከመጥቀስ ባለፈ እርሱ ግን ለማይመራበት ጽሑፍ ምላሽ እንሰጣለን።
በ“መድሎተ ጽድቅ” ገጽ 46 ላይ «1.2 መኃትወ ታሪክ ዘመናፍቃን» በሚለው ዐቢይ ርእስ ሥር በሚገኘው «1.2.1.1 ሃይማኖት ምንድነው?» በሚለው ንኡስ ርእስ ሥር ስለ ሃይማኖት ምንነት በቀረበው ሐተታ ውስጥ የተነሡ አንዳንድ ነጥቦችን እንመለከታለን። በመጀመሪያ የምንመለከተው፣ “እግዚአብሔር ሃይማኖትን ሰጠ እኛ ደግሞ ተቀበልን። የሰው ልጅ ሃይማኖትን ይቀበላል እንጂ ሃይማኖትን ሊሠራ ወይም ሊያሻሽል አይችልም። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት’ በማለት የገለጸው ይህን ነው። ዮሐ. 17፥8 እንዲሁም ‘ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው’ ያለው ለዚህ ነው። ስሙንም ማንነቱንም ሊገባን በሚችለው መጠን የገለጠልን ራሱ እግዚአብሔር ነው እንጂ ሃይማኖት የሰው ልጅ በምርምር የደረሰበት አይደለም። ዮሐ. 17፥6።

Thursday, March 12, 2020


“ወንሕነሰ  ንሰብክ  ክርስቶስሃ  ዘተሰቅለ”
“እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” (1ቆሮ. 1÷23)

የስብከተ ወንጌል ሥራ ሲታሰብ “መሰበክ ያለበት ማነው?” የሚለው ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ነው። በየሃይማኖቱ የሚሰበኩ ልዩ ልዩ አማልክትና አዳኞች ይኖራሉ። በክርስትና የሚሰበከው አዳኝ ግን አንድ ብቻ፣ እርሱም ሰው የኾነውና የተሰቀለው አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከእርሱ በቀር የሚሰበክ ሌላ አዳኝ የለም። ከእርሱ በቀር ሌሎችን “አዳኞች” አድርጎ የሚሰብክ ሰማያዊ መልአክም ኾነ ምድራዊ ሰው ቢኖር፣ ያ ልዩ ወንጌል ነውና እርሱ በሐዋርያት ቃል ውጉዝ ነው (ገላ. 1፥6-9)። 

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስ መስቀል ከንቱ  እንዳይኾን ወንጌልን  እሰብክ ዘንድ ልኮኛል፤ የምሰብከውም በቃል ጥበብ ወይም “በሰዎች የንግግር ጥበብ” (ዐመት) አይደለም ይላል (1ቆሮ. 1፥17)። ይህም ወንጌሉ ከመስቀሉ ሥራ ጋር በጥብቅ የተቈራኘ መኾኑን ያስረዳል። የምንሰብከውም ሌላውን ሳይኾን “የተሰቀለውን” ክርስቶስን ነው። የመስቀሉ ቃል ወይም “ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ” የሚለው ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ቢኾንም፣ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኀይል ነውና።

Sunday, March 8, 2020

ማስታወቂያ


ጮራ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ለንባብ ትበቃለች።

Monday, January 27, 2020

ከዓለመ መጻሕፍት


ሃይማኖተ አበው ቀደምት
ካለፈው የቀጠለ

ነገረ ክርስቶስን በምልአት አብራርተዋል
ክርስትና በፍሬምናጦስ አማካይነት በኢትዮጵያ ከተሰበከበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዐፄ ሱስንዮስ ዘመን ድረስ የነበረው የተዋሕዶ ባህለ ትምህርትቃልና ሥጋ በተዋሕዶ ወልድ ዋሕድ አካል ልጅ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው። በተዓቅቦ ባሕርያት ግብራት የባሕርይ ልደታት ወልደ አብ በመለኮቱ (በመለኮቱ የአብ ልጅ) ወልደ ማርያም በትስብእቱ (በሰውነቱ የማርያም ልጅ) አብ ቀባዒ (ቀቢ) ወልድ ተቀባዒ (ተቀቢ) መንፈስ ቅዱስ ቅብ (ቅብዐት) ሥግው ቃል (ሥጋ የኾነው ቃል) በተዋሕዶ ገንዘብ ባደረገው በሥጋ ርስት በሥጋ ባሕርይ መንፈስ ቅዱስን ከአብ ተቀበሎ ተቀብቶ፥ በቅባት መሲሕ ወበኵር (መሲሕና በኵር) በኵረ ልደት ለኵሉ ፍጥረት (ከምእመናን ኹሉ በጸጋ ልጅነት የመጀመሪያ ልጅ) ዳግማይ አዳም (ኋለኛው አዳም) ንጉሠ ነገሥት ሊቀ ካህናት፤ ነቢይ ሐዋርያ፣ ላእክ መልአክ (አገልጋይ መልእከተኛ) ኾነ ወይም ተባለ ማለት ነው።ይላሉ።ይህ ኹሉ በቅባት የሚሰጥ የሹመትና የግብር ስምሲኾን ከመቀባቱ ጋር ተያይዞ መሲሕነቱን አምልቶ አስፍቶ አጕልቶ የሚያሳይ ነው።

ባህለ ትምህርታቸው ተዋሕዶ ኾኖ ሳለ በካሮችና ቅብዐቶች ስማቸው ተቀምቶየጸጋ ልጆችአንዳንድ ጊዜምሦስት ልደትየተሰኙት ለክርስቶስ ኹለት የባሕርይ ልደታት፣ አንድ የግብር ልደት በድምሩ ሦስት ልደታት አሉት ብለው ስለሚያምኑና ስለሚያስተምሩ ነው። ኹለቱ የባሕርይ ልደታት የሚባሉትም ወልድ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት የተወለደው ልደትና ድኅረ ዓለም ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት የተወለደው ልደት ነው። ስለዚህ ወልድበአምላክነቱ የአብ የባሕርይ ልጅ፥ በሰውነቱ የማርያም የባሕርይ ልጅ፥ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰብእ፥ ወልድ ዋሕድነው። በመጀመሪያው ልደት ወልድ የአብ የባሕርይ ልጅ ነው፤ለአብ ወልድ ዘበአማን (የባሕርይ ልጅ) በሚባልበት በአባቱ ባሕርይ ለማርያም ወልድ ዘበአማን (የባሕርይ ልጅ) አይባልም፤ ጌታዋ ፈጣሪዋ እንጂ። እንደዚሁ ደግሞ ለማርያም ወልድ ዘበአማን በሚባልበት በናቱ ባሕርይ ለአብ ወልድ ዘበአማን አይባልም፤ ዘበጸጋ (የጸጋ ልጅ) እንጂ።ይላሉ።