Sunday, August 25, 2013

ማስታወቂያ


ጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቍጥር 45 ለንባብ በቅቷል




*   ርእሰ አንቀጽ
“ደጁ ለጌታ ይከፈት” በሚል ርእስ በቀረበው መልእክት ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ከውስጧ አውጥታ በደጅ ያቆመችውንና “ክፈችልኝ” እያለ የሚያነኳኳውን ጌታዋን እንድታስገባው ጥሪ ያስተላልፋል፡፡ እንዲህ በማለት፦
“የክርስቶስ ሙሽራ የሆንሽ ቤተ ክርስቲያን ሆይ! የክርስቶስ ብቻ እንጂ የሌሎች ልትሆኚ አይገባሽም። በአፍኣ ቆሞ ለሚያንኳኳውና ከአንቺ ጋር እራት ለመብላት ለሚፈልገው ለውድሽ ለክርስቶስ ደጁን ክፈቺለትና ወደ አንቺ ይግባ ማለት እንወዳለን። የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና ደጁን ለጌታ የዘጉበትንም ሁሉ ከዘማሪ ዳዊት ጋር በመተባበር፣ ‘እናንት መኳንንቶች፥ በሮችን ክፈቱ፥ የዘላለም ደጆችም ይከፈቱ፥ የክብርም ንጉሥ ይግባ’ እንላቸዋለን።”

መሠረተ እምነት
“ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም” (2ቆሮ. 5፥16) የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ለስሕተታቸው መሸፈኛነት በተሳሳተ መንገድ እየጠቀሱ፣ የክርስቶስን መካከለኛነት እያስተባብሉና የተዋሕዶን ትምህርት እየበረዙ ላሉ ወገኖች ትምህርተ ተዋሕዶን መሠረት ያደረገ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡

*  የዘመን ምስክር
የዚህ ዕትም የዘመን ምስክር አባ ወልደ ትንሣኤ ግዛው በኋላም ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ እና ሀብተ ስብከት ለብዙ ምእመናን በረከት ሆነው ማለፋቸው የተዳሰሰበት ጽሑፍ ቀርቧል፡፡ “እኔ ሰው ሲፈወስ ደስ ይለኛል፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የፈውስ ስጦታ እንዲሰጠኝ በልጅነቴ ለምኜው ነበር። እግዚአብሔርም የለመንሁትን ሰጥቶኛል። እኔም በክርስቶስ ኀይል የታመሙትን እፈውሳለሁ፥ ለወደ ፊቱም በዚሁ ሥራዬ ለመቀጠል እፈልጋለሁ” ማለታቸው ተዘግቧል፡፡

 ፍካሬ መጻሕፍት
    “ልጆችዋ ይነሣሉ፥ ምስጋናዋንም ይናገራሉ … መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ፥ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።” (ምሳ. 31፥28፡29) ለሚለው ጥቅስ ዐውዳዊ ፍቺ ተሰጥቷል፡፡ ጥቅሱ በተሳሳተ አተረጓጐም ለማርያም የተሰጠበትን መንገድ በመፈተሽ ጥቅሱ ለማርያም የተነገረ አለመሆኑን ዋቢዎችን በመጥቀስ ይሞግታል፡፡

*  ታላላቅ መንፈሳውያን ቃላት
ፍቅር የተሰኘውን መንፈሳዊ ቃል የሚያብራራ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ቀርቧል፡፡

ሌሎችም ጽሑፎች የተካተቱበትን ጮራ መንፈሳዊ መጽሔት ቊጥር 45ን ገዝተው ቢያነቡ ትልቅ መንፈሳዊ በረከት እንደሚያገኙ ጥርጥር የለንም፡፡

1 comment:

  1. የሰይጣን ጮራ ። አንድ ቢሊዮን ሉተራዊ ቢንጫጫ ድንግሊቱ የረገጠችውን አቧራ የሚያክል ክብር የለውም። ፓስተር ዲያብሎስ ሆይ ምንም አታመጣም። ድንግሊቱ አንዴ ተመርጣለች ። ሉተርዬ ራስህን ስቀል

    ReplyDelete